እግዚአብሔር እኛን ከፈጠረበት አንዱ ምክንያት ከእርሱ ጋር ህብረት እንድናደርግ ነው። ለዚህም ነው '' በመልካችን እንደ ምሳሌአችን '' እንፍጠር (ዘፍ 1፥26) ያለው። ከእርሱ ጋር ብቻ ሳይሆን ሰው ብቻውን ይሆን ዘንድም መልካም እንዳልሆነ በመናገር አጋር እንደሚያስፈልገው ስላወቀ የሚመቸውን ረዳት ፈጠረለት። ሰው ብቸኛ መሆን እንደሌለበት ከፍጥረቱ መረዳት ይቻላል።
በመፅሐፍ እንደምናነበው ሰው ብቻውን ሲሆን መልካም ያልነው በኅብረት ሲሆን ደግሞ በዛው ልክ መልካምና ያማረ ነው። እንዲህ ተብሎም እንደተፃፈ
'' ወንድሞች በኅብረት ቢቀመጡ፥ እነሆ፥ መልካም ነው፥ እነሆም፥ ያማረ ነው። ከራስ እስከ ጢም እንደሚፈስስ፥ እስከ አሮን ጢም፥ በልብሱ መደረቢያ እንደሚወርድ ሽቱ ነው። በጽዮን ተራሮች እንደሚወርድ እንደ አርሞንዔም ጠል ነው፤ በዚያ እግዚአብሔር በረከቱን ሕይወትንም እስከ ዘላለም አዝዞአልና። '' (መዝ 133፥1-3)
አሮን በበረሃ ጉዞ ላይ በሊቀካህንነት ሲሾም የበረሀው ንዳድ ያደረቀውን በራሱ ላይ የፈሰሰው ዘይት ራሱን እንዳረሰረሰው መልካም፣ በበረሀ ያለው አድካሚ ጉዞ አልቦ የሰውነትን ጠረን እንደሚቀየር በልብሰ ተክህኖውም ላይ ያማረ ልዩና ጥሩ መአዛ ያለው ሽቱ እንደተረጨው መልካም፣ የበረሀ ንዳዱ ከፍተኛ የውሃ ጥምን ባመጣ ጊዜ ከበረዶሃማ ተራራ ጫፍ ላይ ጥምን የሚያረካ ቀዝቃዛ ውሃ እንደሚወርድ መልካም የወንድሞ በህብረት መሆን እጅግ መልካም ነው።
በሌሎች መሰብሰብ ውስጥ የማይገኝ በዚህ በወንድሞች በኅብረት መቀመጥ ብቻ ለዘላለም የታዘዘ በረከትና ሕይወት እግዚአብሔር አዟል። ይህ ደግሞ እንዴት ያለ መልካም ነገር መሆኑ ይበልጥ ያሰረዳል።
እንደ ልቡ ሀሳብና ምክር መቀመጥ ይሁንልን።
ነገር ግን እግዚአብሔር በምሕረቱ ባለ ጠጋ ስለ ሆነ፥ ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ በበደላችን ሙታን እንኳ በሆንን ጊዜ ከክርስቶስ ጋር ሕይወት ሰጠን፥ በጸጋ ድናችኋልና፥ ኤፌ 2፥4-5
Monday, 30 December 2019
የመንገድ ላይ መድሃኒት
ኢየሱስ የሚለው ስም በየመንገዱ ሲጠራ ደስ የማይላቸው ብዙ ሰዎች እንዳሉ መናገር የሚከብድ ነገር አይደለም። በአብዛኛው ሰዎች ሞቅ ባለ ጨዋታቸው ይሁን በስራ ጊዜአቸው ሊሰሙት የማይፈልጉት ስም ጥራ ብትሉኝ ይህን ስም ብቻ ነው።
በሀገራችን በተለያዩ ስፍራዎች ከወዳጆቻችን ጋር ተሰብስበን የማውራት ልማድ አለን። በእነዚህ መሰል ጊዜአት የማይነሳ ርዕሰ ጉዳይ አይኖርም ብንል ማጋነን አይሆንም። ፖለቲካ ቢሉ ሃይማኖት፣ ቅልድ ቢሉ ፌዝ፣ የስራ መቀዝቀዝ ቢሉ የኑሮ ውድነት፣ ሽንኩርት ቢሉ ዘይት፣ ዘፋኝ ቢሉ ተዋናይ፣ ደራሲ ቢሉ ፈላስፋ፣ ሜሲ ቢሉ ሮናልዶ፣ አርሴናል ቢሉ ማንቼ፣ ሀይሌ ቢሉ ደራርቱ፣ የሃይማኖት አባት ቢሉ ሰይጣን ጭምር ብዙ አልባሌ ነገሮች............ ብቻ የማይወራ የለም። ሁሉም ጫወታ ይወዳል ጆሮውን ቀስሮ ያዳምጣል የሚያስቅ ያስቀዋል።
በዚህ መሀል ድንገት ስለ ኢየሱስ ከተነሳ ወይም አንድ ሰው በአቅራቢያ ሆኖ ይህን ስም እየጠራ ሰዎች ወደ እግዚብሔር እንዲቀርቡ የማንቂያ ደውል ለማሰማት ከመጽሐፍ ቅዱስ እየጠቀሰ ብቸኛ አዳኝነቱን (መድሃኒትነቱን)፣ እውነተኝነቱን፣ መንገድነቱን፣ ተስፋነቱን፣ አጽናኝነቱን መናገር ሲጀምር አታስዋሹኝ ብዙ ፊቶች መቀያየር ይጀምራሉ። ከፊል ፊቶች እንደ ቲማቲም ይቀላሉ ከፊሉ ደግሞ ጥርሱን ያፏጫል አንዳንዱም ሊማታ ይዳዳውል።
ስለቀልድና ዋዛ ፈዛዛው ቦታ ሳይመርጥ ሲያውካካና ሲያሽካካ የነበረ ስለ ኢየሱስ መስማት ቦታ ያጡና '' ወንጌል ቦታ አለው '' በማለት ይደነፋሉ። ጭራሽ ጫወታችንን አታበላሽ ብለው የሚያጉረመርሙም አይጠፉም። ስለፖለቲካ ፣ ፌዝ፣ እርባና ስለሌለው ቀልድና ስለብልግና ማውራት እንደጥሩ ጫወታ ተቆጥሮ ስለ ኢየሱስ መስማት ግን ጫወታን እንደማበላሸት ሆኖ የሚቆጠርባቸው ጊዜአት ብዙ ናቸው።
ዘፈንና ቀልዱ፣ ቧልትና ፌዙ ሲነገር ሁሉ ያለምንም ልዩነት አንድ ሆነው ሲስቁና ሲፈነድቁ እንዳልነበር '' ኢየሱስ '' የሚለው ስም ሲጠራ የሚበሳጩበት ምክንያት ምንድነው? ዛሬም ድረስ የሚያሳዝነኝ ጥያቄ ነው። ስለ ምድራዊ ነገር ማውራት ለሁሉም የተፈቀ ተግባር ለሰው ልጆች ሁሉ ስለሞተው ስለ ኢየሱስ ብቸኛ መድሃኒትነት መናገር ደግሞ ለተወሰኑ ሰዎች ብቻ የተሰጠ ስጦታ ሆኖ መመስከርን የሚያስወቅስ ተግባር ሆኖ የሚቆጠርበት ምክንያት መኖር ይበልጥ ያሳዝነኛል። በምድራዊ ጉዳይ ሽንጡን ገትሮ የሚከራከር ስለ ኢየሱስ ሲሆን ግን ራሱን ያገላል።
ብዙ ኢትዮጵያዊያን ወንጌል በመንገድ ተመስክሮልን እንደተቀበልነው ይስማማሉ ነገር ግን በመንገድ ላይ ከተነገረን ወንጌል ይልቅ ወንጌሉን ስለ ተቀበለው ሰው ማቀንቀን ይቀናናል። ስለ ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ በስፋት ይነገራል ግን እንዴት ባለ ሁኔታ እንደተቀበለው ልብ የሚል አናሳ ነው። ኢትዮያዊው ጃንደረባ ፊልጶስ ስለ ኢየሱስ በመንገድ ከሰበከለት በኃላ የነበረው ምላሽ ሁለት ነው ጥምቀትን መሻቱና በልቡ ደስ ተሰኝቶ መመለሱ እንጂ ስፍራው አይደለም፣ የእናትና አባቴን ሃይማኖቴ ተከትዬ ከኢትዮጵያ ኢየሩሳሌም ድረስ ለስግደት ያስመጣኝን፣ ተራራ የወጣሁበትን፣ ዳገት ቁልቁለቱን የወረድኩበትን፣ ወንዝ የተሻገርከበትን፣ ይህን ምድር የረገጥኩበትን፣ ታላቅ የበረከት ጉዞ አድርጌ ከመመለስ ባለፈ የእናንተን ኢየሱስን ለመስማት አልመጣሁም ብሎ ፊት አልነሳም። ይልቅስ ለመስማት እጅጉን ጓጓ።
ስለ ኢየሱስ መስማት ደስ የሚያሰኝ እንጂ የሚያስኮርፍም የሚያሳፍርም አይደለም። በመፅሐፍ እንደተፃፈ የኤማሁስ መንገደኞችን ብንመለከት ስለ ኢየሱስ ሲሰሙ የተሰማቸውን እኛም በዘመናችን ሊሰማን ያስፈልጋል።
" እርስ በርሳቸውም። በመንገድ ሲናገረን መጻሕፍትንም ሲከፍትልን ልባችን ይቃጠልብን አልነበረምን? ተባባሉ። "
(የሉቃስ ወንጌል 24: 32)
ከጥቂት ጊዜአት ጀምሮ ብዙ ሰው በሚያልፍባቸው ስፍራዎች በተለይ በገበያ አካቢዎች ቀልቤን የሳበው ነገር ቢኖር '' ዘራ መድሃኒት '' እየተባለ ስለሚሸጠው የአይጥና የበረሮ መርዝ ነው። የዚህ መድሃኒት ማስታወቂያን ልብ ብላችሁ ካዳመጣችሁት '' ታላቅ የምስራች '' ብሎ ነው የሚጀምረው እውነት የቱ መድሃኒት ነው ታላቅ የምስራች?
የማያናድደው? ቦታ ማይገድበው? የማያበሳጨው? የማያስቆጣው?
እኔ እያወራውት ያለሁት ከኃጢአት የሚያድን እርሱን ብቻ በማመን የዘላለም ሕይወት ስለሚያስገኘው ኢየሱስ ነው። ስለ ዘራ መድሃኒት ሲሰማ ያልተሸማቀቀው ጆሮ ኢየሱስ ስለሚባለው መድሃኒት ጆሮውን የሚያከው ለምንደነው? እስኪ መልሱልኝ?
የሰማይ ማስተዋል በኢየሱስ ለኢትዮጵያዊያን ይብዛ አሜን።
Thursday, 19 December 2019
የፍቅር ሽፋኑ
ለሰው ልጅ ለኑሮው እጅግ በጣም አስፈላጊ ነገሮች ውስጥ በዋነኛነት ከሚጠቀሱት ውስጥ ልብስና መጠለያ ናቸው። ሁለቱም የሰውን ልጅ ከተፈጥሮና ከእይታ የሚከልሉ ወሳኝ ነገሮች ናቸው። እንደው በአጠቃላይ እኛ ሰዎች ስንባል፤ ካልተሸፈንን መኖር እንደማንችል ከሚያስፈልገን ነገሮች መረዳት እንችላልን። ህልውናችንም የሚቀጥለው በመሸፈን ውስጥ ነው ብንል ይቀላል። ማንም ከእንቅልፉ እንደተነሳ ራቁቱን ወደ ውጭ አይወጣም ወይም መሸብኝ ብሎ መንገድ ዳር አይተኛም።
የመጀመሪያ ፍጥረታት የሆኑት አዳምና ሄዋን ከተላለፉ በኃላ በመጀመሪያ ያደረጉት ነገር ቢኖር ራሳቸውን መሸፈን ነበር። በበለስ ቅጠል ግልድም አሰሩ ከዚያ ጊዜ ጀምሮ በዘመናችን ጅንስ እስከምንለው ድረስ ሁሉም ሰውነቱን በመሸፈን ይኖራል። እግዚአብሔር ግን መልካም ነውና የሰው ልጅ ያገለደመው ቅጠል ቶሎ የሚደርቅ በመሆኑ የልጁን መሰዋት ምሳሌ በማድረግ ዘላቂውን ቁርበት አለበሳቸው።
ይህ በሥጋ መሸፈን ዛሬም የሚያስፈልግ ቢሆንም እንኳ አዳምና ሄዋን ያደረጉት ቅጠል የሰውን ጽድቅ ያሳያል። እንደ ጠዋት ጤዛ ታይቶ የሚጠፋ፣ በቶሎ የሚደርቅ፣ አለ ሲባል የሌለ ነው። ሁሉቱም ይህን ሲያደርጉ መንፈሳዊ ስሌት የሌለበት ሥጋን ብቻ ያተኮረ መፍትሄ ነበር የወሰዱት እግዚአብሔር ግን ጉዳዩን ቀየረው እንጂ። ቁርበት የእግዚአሔርን ጽድቅ ሲወክል ዘላቂነትንም የሚያሳይና መሸፈን ለሚያስፈልገው ማንነት በመስዋህትነት የሚቀርብ ሥጦታ እንደሆነ መረዳት እንችላልን።
ከብሉይ ኪዳን የጽድቅ ስራዎች ተብለው ከሚዘረዘሩት ውስጥ አንዱ ማጋለጥ ነው። ሕጉ በሚያዘው መጠን መጋለጥ ያለበት ነገር፣ መውጣት ያለበት፣ መነገር ያለበት ወሬ ያለ ርእራሄ እስከ ሞት ድረስ እንኳ ዋጋ ቢያስከፍል ጉዳዩ ለእስራኤል ሕዝብ ይጋለጣል። እንዲህ ተብሎ እንደተፃፈ ማንም ሌሎች አማልክት እናምልክ ብሎ ቢያስትህ፥ እሺ አትበለው፥ አትስማውም፤ ዓይንህም አይራራለት፥ አትማረውም፥ አትሸሽገውም፤ ነገር ግን ፈጽመህ ግደለው፤ (ዘዳ 13፥6-10)
ለአብነት ያህል ሌላ ከዚሁ ከዘዳግም መፅሐፍ አንድ ምሳሌ እንውሰድ:-
ማንም ሰው ለአባቱ ቃልና ለእናቱ ቃል የማይታዘዝ ቢቀጡትም የማይሰማቸው እልከኛና ዓመፀኛ ልጅ ቢኖረው፥ አባቱና እናቱ ይዘው ወደ ከተማው ሽማግሌዎች ወደሚኖሩበትም ስፍራ በር ያምጡት፤ የከተማውንም ሽማግሌዎች። ይህ ልጃችን እልከኛና ዓመፀኛ ነው፥ ለቃላችንም አይታዘዝም ስስታምና ሰካራም ነው ይበሉአቸው። የከተማውም ሰዎች ሁሉ እስኪሞት ድረስ በድንጋይ ይውገሩት፤ እንዲህም ክፉውን ነገር ከመካከልህ ታርቃለህ፥ እስራኤልም ሁሉ ሰምተው ይፈራሉ። (ዘዳ 21፥18-21)
ሕጉ የሚያሳየው ምን ያህል ማጋለጥ ዋጋ ያለው ነገር እንደሆነ ነው። ወላጆች ልጆቻቸውን እንኳ ለሞት አሳልፈው እስኪሰጡ ድረስ የሚያሰጨክን የማጋለጥ ስራ የታዘዙበት ሕግ ነው። ነገር ግን ማጋለጥ ብቻ እውነት አይደለም ይልቁንስ መሸፈን በሙላት የሚሰራ እግዚአብሔር ያዘጋጀው የአዲስ ኪዳን ጽድቅ ነው። አዳምንና ሄዋንን በቁርበት የሸፈነው እርሱ የዓለምን ኃጢአት ሁሉ ውድ ልጁን ኢየሱስን በመስጠት ከድኖታል።
መፅሐፍ እንደሚል "፤ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና። " (ዮሐ 3፥16) ይህ መውደድ ነው የዓለም ኃጢአት የሸፈነው። የሰው ልጅ የኃጢአቱ ብዛት ግንባሩ ላይ ቢፃፍ አይደለም ከእግዚአብሔር ፊት ሊቆም፤ እርስ በራሳችን እንኳ ለመተያየት ባልደፈርን ነበር። መወደድ ያመጣው መሸፈን ማለት ይህ ነው። እግዚአብሔር ስሙ ይባረክ በባሕሪው ሸፋኝ ነው። እንዲህ ተብሎ እንደተፃፈ " የእግዚአብሔር ክብር ነገርን መሰወር ነው፤ የነገሥታት ክብር ግን ነገርን መመርመር ነው። " (ምሳ 25፥2)
መሸፈን የኢዲስ ኪዳን ጽድቅ ነው። ክርስቲያን ከክርስቲያን ጋር በሚኖረው ግንኙነት ውስጥ አንዱ ቢበድለው በመጀመሪያ ብቻውን ያናግረው የተባለውም መሸፈን ስላለብን ነው። በማጋለጥ ውስጥ ብዙ ትርፍ አለው ለዚህም ቀዱሱ መፅሐፍ ሲመሰክር '' ወንድሞቼ ሆይ፥ ከእናንተ ማንም ከእውነት ቢስት አንዱም ቢመልሰው፥ ኃጢአተኛን ከተሳሳተበት መንገድ የሚመልሰው ነፍሱን ከሞት እንዲያድን፥ የኃጢአትንም ብዛት እንዲሸፍን ይወቅ። '' (ያዕ 5፥19-20)
ዛሬ ላይ ሰው ለሰው የማይተኛበት ዘመን ላይ ነን። በምዕራባዊያን ዘንድ እንደተለመደው የሰውን ገመና ፈልፍሎ እንደሚያወጣው ፓፓራዚ የሰውን ምስጢር መጠበቅ አቅቶን ጭራሽ ገመና ፈላጊዎች ሆነናል። ጌታ ኢየሱስ ማስተዋል ያብዛልን። ስለ ሰው ድካም መቁጠር አቁመን የተተወልልን በደላችንን እያሰብን፣ የቀረልንን ቁጣ እያሰላሰልን አመስጋኝ እንድንሆንና አንድ ሰው በድካም ውስጥ ብናየው ያ ሰው እንዲመለሰ የፀሎት ርዕስ እንዲሆነን እመክራለው።
" ትጸልዩም ዘንድ በመጠን ኑሩ፤ ፍቅር የኃጢአትን ብዛት ይሸፍናልና ከሁሉ በፊት እርስ በርሳችሁ አጥብቃችሁ ተዋደዱ። " (1ኛ ጴጥ 4፥8) እዚህ ላይ ማስተዋል ያለብን '' ከሁሉ በፊት '' የሚለውን ኃይለ ቃል ነው። አዎ ከምንም በፊት ፍቅር ይቀድማል። በሌላ ስፍራ እንደምናነበው ፍቅር ግን ከሌለኝ ከንቱ ነኝ እንደሚል ለየትኛውም የመንፈሳዊ ሕይወት እንቅስቃሴ ይህ ፍቅር መሰረት ነው። ይህ ፍቅር ሲኖረን ነው የወዳጆቻችንን ሰንፍና የምንሸፍነው። ከላይ እንዳነበብነው ፍቅር የኃጢአትን ብዛት የመሸፈን አቅምና ጉልበት አለው። ስለተሸፈነልን እንሸፍን። በመሸፈን ውስጥ እጅግ ብዙ ትርፍ አለና።
ጌታ ኢየሱስ በቀራኒዮ መስቀል ላይ ያፈሰሰው ደም ከፍቅር የተነሳ ነው። " ነገር ግን ገና ኃጢአተኞች ሳለን ክርስቶስ ስለ እኛ ሞቶአልና እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን የራሱን ፍቅር ያስረዳል። " (ሮሜ 5፥8) የዚህን የክርስቶስ ኢየሱስ ፍቅር ስፋቱና ርዝመቱ ከፍታውም ጥልቅነቱም ምን ያህል መሆኑን ለማስተዋል፥ ከመታወቅም የሚያልፈውን ለማወቅ እንበረቱ ዘንድ ዓለምን የሞላት የእርሱ ጸጋ ሁላችንንም ይርዳን አሜን።
በየትኛውም ስፍራ በማንኛውም ሰዓት ሁሉም ሰው ማየት ያለበት ይህን ፍቅር ነው። ዓለምን በደሙ የከደነ የኢየሱስ ደም ዛሬም ትኩስ ነው ከኃጢአት ያነፃል፣ በደልን ይሸፍናል፣ አዲስ ሰው ያደርጋል፣ ለዘላለም ያድናል።
Friday, 8 November 2019
የትዕግሥት ጥግ
ትዕግሥት :- ይቅር ባይ፣ ልበሰፊ ፣ ቻይ ፣ትሁት የሆነ የጠባይ መለያ ነው።
ከሰው ጋር ከግንኙነት ነፃ በማንሆንበት በዚህች ዓለም ስንኖር አስፈላጊ ነገር ከሆኑት መካከል አንዱ ትልቁ ትዕግሥት ነው። በዚች ምድር ሰፊውን የሕይወታችንን ክፍልንም የሚይዘው ነገር ደግሞ ግንኙነት ነው። ታዲያ በዚህ ሰፊ ግንኙነት ውስጥ ከሚያስፈልገን ነገር አንዱ ይህ ትዕግሥት ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ስለ ትዕግሥታቸው ከሚጠቀስላቸው ሰዎች አንዱ ደግሞ በሁላችንም ህሊና ውስጥ የሚመጣው ኢዩብ ነው።
''ወንድሞች ሆይ የመከራና የትዕግሥት ምሳሌ የሆኑትን በጌታ ስም የተናገሩትን ነብያትን ተመልከቱ። እነሆ፥ በትዕግስት የጸኑት ብፁዓን እንላቸዋለን፤ ኢዩብ እንደታገሰ ሰምታችኋል፥ ጌታም እንደፈፀመለት አይታችኋል፤ ጌታ እጅግ የሚምር የሚራራም ነውና።'' (ያዕ 5፥10-11)
በዚህ ቃል መሠረት፥ ከላይ እንደገለፅኩትም ኢዩብ በትዕግሥቱ በሁላችንም ህሊና የማይጠፋና ለብዙ ጊዜያትም በምሳሌነት ሲነሳ የምናውቀው ቢሆንም ኢዩብ በታገሠው ትዕግሥት ከብጹዓን ቢመደብም ድካም ( ስንፍና ) ግን ነበረበት
'' ከዚያም በኋላ ኢዩብ አፉን ከፍቶ የተወለደበትን ቀን ረገመ። ..................'' (ኢዩ 3፥1 ጀምሮ) ይህም በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ያለውን ቃል ሲተላለፍ እና የነበረውን ፅናት ስፍራ አስለቅቆታል።
'' ግሩምና ድንቅ ሆኜ ተፈጥሬአለሁና አመስግንሃለሁ፤ሥራህ ድንቅ ነው፣ ነፍሴም እጅግ ታውቀዋለች።'' (መዝ 138፥14) የሚለውን ዘነጋና ሞቱን ተመኘ መፈጠሩንም ረገመ። በብዙ ችግር ውስጥ ቢሆንም ግን የትዕግሥት ልኩ ታየ።
ሰ
ትዕግሥት ካደረግን ሊመጣ (ሊፈፀም) የሚችል ታላቅ ኋጢአት ሁሉ በድል የምናልፍበት አቅም እናገኛል። በትዕግሥት ውስጥ በመቆየታችን ለችግራችን የሚሆን የመፍትኤ ሀሳብ ይበዛልናል በመሆኑም ተቻኩለን ከምናደርጋቸው ድርጊቶች ይልቅ በዝግታ አስበን የምናገኘው መፍትሄ የተሻለ ነው።
ማንም እንኳ ኢዮብ ታጋሽ መሆኑን የተመሰከረለት ቢሆንም እንደውም ''ትዕሥት እንደ ኢዮብ ስጠን'' እየተባለ ሲነገር ብንሰማም በእሱ ላይ መቆም እንደሌለብን እሙን ነው ምክንያቱም ኢዩብ ከታገሠው ትዕግሥት የሚልቅ ወይም ከኢዩብ አልፈን ልናወራለት፣ ልንመሰክርለት፣ ልንመለከተው እንዲሁም ልናስተውለው የሚገባን ሌላ ታጋሽ አለን። ሌላ ልናወራለት የሌለ የትዕግሥት ጥግ አለን። ኋጢያት የማያውቀው ወደር የሌለው የትዕግሥት ምሳሌ አለን።
'' ስለዚህ፥ ከሰማያዊው ጥሪ ተካፋይ የሆናችሁ ቅዱሳን ወንድሞች ሆይ፥ የሃይማኖታችንን ሐዋሪያና ሊቀ ካህናት ኢየሱስ ክርስቶስን ተመልከቱ፤ '' (ዕብ 3፥1) ተብሎ እንደተፃፈ፥ ስለ ትዕግሥት ስናስብ ከኢዩብ የሚበልጠውን የኢየሱስ ክርስቶስን ትዕግሥት መርሳት የሌለብን።
(የመልእክቴም ዋና ሀሳብ ይህ ነው) ስለ ሁላችን ኃጢአት ሳይገባው መከራን ሲቀበል፣ በሌለበት በደል ሲከሰስ በሸላቾች እንደሚታረድ በግ ዝም ሲል፣ በቁስሉ ቁስላችንን ሲያክም፣ በቀራኒዮ በደሙ ሲዋጀን፣ በእርጥብ እንጨት ላይ በችንካር ሲሰቃይ፣ በተጠማው አንጀቱ ሆምጣጤ ሲጠጣ፣ እንደ ወንበዴ በመስቀል ሲሰቀል፣ በበደልና በኋጢአታችን ሙታን የነበርነውን ጽድቃችንም የመርገም ጨርቅ የሆነብን ስለእያንዳንዳችን ሞታችንን በሞቱ በትዕግሥት ሲሽር ከእግዚአብሔር ያጣነውን ልጅነት አስገኘን። ይህም የኢየሱስ ፍቅር ምን ያህል ታላቅ እንደሆነ ያሳየናል እንድም አፀፋ ሳይመልስ ሁሉ ታግሶ መዳናችንን ፈፅሞልናል።
'' የጌታችንም ትዕግሥት መዳናችሁ እንደ ሆነ ቁጠሩ '' (2ኛ ጴጥ 3፥15)
ሰለዚህም ዩሐንስ በፍጥሞ ደሴት ሳለ '' መከራውንና መንግስቱን የኢየሱስ ክርስቶስን ትዕግሥት የምካፈል'' እንዳለው ልንካፈለው የሚገባን የትዕግሥት ጥግ ከኢዩብ የላቀውን፣ አልፈን የማናወራለትን የኢየሱስን ትዕግሥት ሊሆን ይገባል።
ደዊት 2008 የምህረት ዓመት የተፃፈ
ተመልከቱ
እርስ በራሳችን በዘልማድ የምንተያይበት መንገድ ልክ አይደለም ብዬ አስባለው። መተያየት ካለብንም የእግዚአብሔር ቃል በሚያዘው መንገድ እንጂ ከልጅነታችን ጀምሮ በኖርንበትና በለመድነው ሁኔታ መሆን የለበትም እላለው። ከመተያየት ውጪ መሆን አይቻልም ምክንያቱም እየኖርን ያለነው በገሀዱ ዓለም ስለሆነ። ዓይናችን ማየት እስከቻለው ድረስ ያማትራል ነገር ግን የምናየውና የምንመለከተው ነገር የተገደበ ነው። ዓይናችን ማየት ከሚችለው በላይ ማየት ፈፅሞ አይችልም። ልክ እንደዚሁ በመንፈሳዊ እይታም ከእግዚአብሔር ቃል ውጪ ልንመለከተው የሚገባ ምንም ነገር የለም።
ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዮሐንስ ወንጌል በምዕራፍ 15፥12 እንደተናገረው
'' እኔ እንደ ወደድኋችሁ እርስ በርሳችሁ ትዋደዱ ዘንድ ትእዛዜ ይህች ናት።''
በዚህ ዓለም በሚኖረን ማንኛውም ዓይነት ግንኙነቶች ውስጥ አንድ ክርስቲያን ከዚህ ትህዛዝ የሚያስወጣው ሌላ ምክንያት ወይም መሰረት የለውም። እርስ በርሳችን ልንሆን የሚገባው ሁሉ ያለ ጉድለት ተፅፏል። እኛ የምንጨምረውም ሆነ የምናካትተው ነገር የለም። በመዋደድ ውስጥ ያሉ መልካምና እግዚአብሔርን ደስ በሚያሰኝ ግንኙነት ውስጥ ሆነን መኖር ይገባናል።
እርስ በራሳችን ልንተያይ የተገባ መንገድ የሌላው ሰው ስህተት ውስጥ መሆን የእኛን ልክነት አይነግረንም፣ የሌሎች ውድቀት እኛን አያነሳም፣ የሌሎች መክሰር የእኛን ማትረፍ አያረጋግጥም፣ የሌላው መጥፎነት የእኛን መልካምነት አያሳይም፣ የሌላው መራብ የእኛን መጥገብ አያሰኝም፣ የሌላው ሞኝነት የእኛን ብልጥነት አይናገርም፣ የሌላው ንፉግነት የእኛን ለጋስነት አያመጣውም። ይልቁንም አንዱ ከሌላው ሊወስደው የሚገባ ያለውን ጥንካሬና ጥሩ ነገሮችን ብቻ ነው። የሰዎችን ስህተት በማየት የምናጉረመርም ካለን ከእነሱ እኛ በምን ተሻልን?
የራሳችንን ብቻ ልክ አርገን የሌሎችን አብጠልጥለን በግንኙነቶች ውስጥ መዝለቅ ከባድ ነው። እኛ አለን ከምንለው ሀሳብ ወይም ተግባር ሌላ ሰው ካለው ነገር ጋር ማነፃፀር ሳይሆን ልክነቱ የራሳችን ሀሳብና ተግባር የሕይወታችን ቱንቢ ወይም መለኪያ በሆነው፣ ሕያውና በሚሰራው ሁለትም አፍ ካለው ሰይፍ ይልቅ የተሳለ ነፍስንና መንፈስን ጅማትንና ቅልጥምን እስከሚለይ ድረስ በሚወጋው የልብንም ስሜትና ሀሳብ በሚመረምረው በእግዚአብሔር ቃል ነው መመዘን ያለብን(ዕብ 4፥12)። ዳኛችን ቃሉ ነው።
ታዲያ የእግዚአብሔር ፈቃድ ቃሉ እንደነገረንና እንዳሳሰበን እርስ በራሳችን ባለን ግንኝነት ባለፈ ልናየውና ልንመለከተው የሚገባ ትልቁ አጀንዳ አለ። እርሱም
የእስራኤል ሕዝብ ከግብፅ ባርነት ወጥተው በጉዞ ላይ እያሉ በእግዚአብሔርና በሙሴ ላይ በማጉረምረማቸው እግዚአብሔር ሕዝቡን እባቦችን በመስደድ አስነድፎ ቀጣቸው ብዙዎች ሞቱ። የተቀሩት ግን ከጥፋታቸው በመመለሳቸው እና በመፀፀታቸው እግዚአብሔርም ሙሴን፦ እባብን ሠርተህ በዓላማ ላይ ስቀል የተነደፈውም ሁሉ ሲያያት በሕይወት ይኖራል አለው። ሙሴም የናሱን እባብ ሠርቶ በዓላማ ላይ ሰቀለ፤ እባብም የነደፈችው ሰው ሁሉ የናሱን እባብ ባየ ጊዜ ዳነ።(ኦሪ ዘኋ 21)
በእባብ ተነድፎ ከሞት የተረፉት ተመልከቱ የባለውን የእግዚአብሔርን ቃል ብቻ በመስማት ነው። ታዲያ እኛም እንደ እንደ እንግዳና እንደ መፃተኛ በምንኖርበት በዚህ ምድረ በዳ ዓለም ልንመለከተው የሚገባን አለ። ለክርስቶስ ኢየሱስ ምሳሌና ጥላነት ያገለገለው በሕግ ኪዳን ዘመን እንኳ እንዴት በመመልከት ብቻ እንደተረፉ አይተናል። አሁንም ደግሞ አካል የሆነው ክርስቶስ ኢየሱስ በመገለጡ በዘላለም ኪዳን ደም የተገዛን የእግዚአብሔር ልጆች ሆነን በሰማያዊ ጥሪ ተቀብለን እንድንኖር የተከፈለልን ክቡር ዋጋ ያለን እኛ የአምላካችን የእግዚአብሔር ፈቃድ ልጁን መድህነ ዓለም ክርስቶስን ኢየሱስን መመልከት ብቻ ነው። እግዚአብሔር በቀራኒዮ አደባባይ ስለሰው ልጅ ኋጢአትና አለመታዘዝ ነውራችንን ወስዶ እርቃኑን የሞተልንን ልጁ ብቻውን እንዲታይለት ይፈልጋል።
ስለዚህ፥ ከሰማያዊው ጥሪ ተካፋዮች የሆናችሁ ቅዱሳን ወንድሞች ሆይ፥ የሃይማኖታችንን ሐዋርያና ሊቀ ካህናት ኢየሱስ ክርስቶስን ተመልከቱ፤ ዕብ 3፥1 ተብሎ እንደተፃፈ።
ተወዳጆች ዓለም ሳይፈጠር በፊቱ ቅዱሳንና ነውር የሌለን በፍቅር እንኖር ዘንድ በልጁ የመረጠን የአባቶቻችን አምላክ ፈቃዱን ታውቅ ዘንድና ጻድቁን ታይ ዘንድ ከአፉም ድምፅን ትሰማ ዘንድ ነውና ብሎ በደማስቆ እንደ እግዚአብሔር ሀሳብና የልቡ ምክር ይኖር የነበረው ሐናንያ ለሐዋርያው ለቅዱስ ጳውሎስ እንደነገረው (ሐዋ 22፥14) ሁላችንም በምድር ላይ ያለን ተልእኮ ጌቱችንና መድሃኒታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን በመመልከት ምስክሮቹ መሆን ነው።
በእግዚአብሔርና በጌታችን በኢየሱስ እውቀት ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ። አሜን
በክርስቶስ ውስጣዊ ራስን መቻል
እግዚአብሔር በእኛ ላይ ካለው ፍላጎት አንዱ በየትኛውም ስፍራ በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ ብንሆን ራሳችንን እንድንሆን ነው። እኔ እከሌን መሆን አልችልም በአንፃሩም እከሌ እኔን አይተካም። በመንፈሳዊ ሕይወታችንም ሆነ በዚህ እንደ እንግዳና መፃተኛ ሆነን በምንኖርበት ኑሮ ራሳችንን ችለን እንድንኖር እግዚአብሔር ይፈልጋል።
አንድ ክርስቲያን በሁለት ገፅታ ውስጥ ለአንድ ዓላማ ይኖራል ይህ ማለት ግን ሁለት ማንነት ይኖረዋል ማለት አይደለም። አንደኛው ገፅታው ኑሮው (ስጋዊ) ሲሆን ሁለተኛው ዘላለማዊ ሕይወት (መንፈሳዊ) ነው። ኑሮ ጊዜአዊና አላቂ ሲሆን በዚህ ምድር ላይ በምንቆይባቸው ዘመናት ውስጥ ለሰውነታችንና ለጤናችን እንዲሁም ከሰው ጋር ባለን ግንኙነት ቤተሰብን ጨምሮ የሚያስፈልገንን ለማግኘት የምናደርገው ውጣ ውረድ ነው። ዘላለማዊ ሕይወት ደግሞ ጌታችን መድሃኒታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን በማመን የሚገኝ የማያልቅና ዘመን የማይሽረው ልዩ መለኮታዊ ስጦታ ነው (ዮሐ 6፥47) (ዮሐ 11፥25/14፥6)። በሚያልፍ ኑሮ ውስጥ የሚገኝ የማያለፍ ዘላለማዊ ሕይወት ያለን ባለ ሁለት ገፅታ ሰዎች ነን።
ታዲያ በሁለቱም ገፅታዎች ራሳችንን ችለን መቆም ያስፈልገናል። በየትኛውም ነገር በማንም ሰው ላይ መደገፍ የለብንም። ይልቁን ልንደገፍበት የሚገባ በድካማችን የሚራራልን፣ ባስፈለገን ጊዜ የሚደርስልን፣ በእጁ መዳፍ የያዘን ዋስትናችን፣ ልናምነው ዘንድ የተገባ ብቸኛ ማረፊያችን እርሱ ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።
እርሱን በማመን የምናገኘው መንፈሳዊ ጥንካሬ ለነገሮች ሁሉ መቻልን ያድለናል። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች በፃፈው መልእከቱ በምዕራፍ 4 ቁጥር 13 ላይ '' ኃይልን በሚሰጠኝ በክርስቶስ ሁሉን እችላለሁ። '' እንዳለው ከውጫዊ ሁኔታዎች ነፃ መሆን ባንችልም ልንጎዳ ወይም በተፅህኖ ውስጥ ሊጥለን አይገባም። የቱንም ያህል ፈተና ቢበዛብን፣ በፍፁም ይሆናል ብለን ያልጠበቅነው ፈተና ፊታችን ድንቅር ቢልም፣ ይሆናል ወይም ይሳካል ያልነው ጉዳይ ከመሆን ቢዘገይም በነዚህ ነገሮች ተይዘን ከመፍትኤ ውጪ መሆን የለብንም ምክንያቱም ውጫዊ እርዳታን የማይጠይቅ ውስጣዊ ራስን መቻል በክርስቶስ አለንና።
ይህን ስል ተማሪ ሳለው በታሪክ ትምህርት ውስጥ ወቅቱንና በማን ዘመነ መንግስት እንደሆነ ማስታወስ የማልችለው የጦነት ታሪክ ትዝ አለኝ። ጦርነት የተለያዩ ስትራቴጂዎች አሉት። እናም ይህን ትዝ ያለኝን የጦነት ስልት ከማወራው ጉዳይ ጋራ እያቃጨለብኝ ስለሆነ ለመፃፍ ተገደድኩኝ።
በአንድ ወቅት ኢትዮጵያዊያን ዘማቾች የተደፈረብንንና የተወሰደብንን ከተማ ለማስመለስ ወደ ቦታው ዘምቶ ነበረ። ታዲያ በወቅቱ የነበረው የዘማቾቹ ፊትአውራሪ ብልህ ስለነበረ ብዙ ድካም ሳያወጣና ደም ሳይፋሰስ እንዴት የጠላትን እጅ መማረክ እንዳለበት አሰበና አንድ ነገር ወሰነ። ጠላት የያዘውን ትንሿን ከተማ ዙሪያውን በመውረር ከተማይቱ የምትጠቀምበትን የውሃ ጉድጉውድ እና ከከተማ ውጪ የምትገኘውን የእህል መጋዘን ተቆጣጠረ። የጠላት የጦር ሰራዊትም በከተማው ውስጥ ያለውን መጠቀም እስኪያስችለው ድረስ መሽጎ ቢቆይም ሰራዊቶቹ ከፊሉ በውሃ ጥም ግማሹ በረሃብ ጠኔ ተመተው በመዳከማቸው ቀስ በቀስ የነበራቸው የመዋጋት ወኔም ደብዛው ጠፋ። በዚህ መሃል እንዳይዋጉ በማጣት ቸነፈር ውስጥ ጉልበታቸውን አጥተዋልና የነበራቸው ብቸኛ ነገር ያለ ውጊያ እጅ መስጠት ነበረና እጅ ሰጥተው ተማረኩ ከተማይቱም በሰላም በአገሬው ልጅ ተጥለቀለቀች።
በዚህ ታሪክ ውስጥ እንደምንረዳው በውጫዊ እገዛ ወይም ጥገኝነት እስካለን ድረስ የሚመጣብንን የዓለም ፈተና ማለፍ አንችልም። ይህች ከተማ በውስጧ የውሃ ጉድጉዋድ እና የእህል አቅርቦት ቢኖራት ኖሮ ወይም ውጫዊ አቅርቦት ባያስፈልጋት ኖሮ ከውጪ ለሚመጣ ማንኛውም ሰልፍ ራሷን ችላ ትመክት ነበረ፣ ለደረሰባት ከበባ ስጋት የተጋለጠች ባልሆነች ነበር። ስለዚህም እኛም እንዲሁ በኑሮ ከዓለም ለሚመጣ ፈተና ኋይልን በሰጠን በክርስቶስ የተጋረጠብንን ማንኛውንም ፈተና በውስጥዊ ራስን መቻል ልንረታው ያስፈልገናል። ደግሞም በሚያስፈልገን ጊዜ የሚረዳን የእግዚአብሔር ፀጋ አለና።
አንድ ሰው በንብ ቢነደፍ ውጫዊ የሰውነት ቆዳን ወይም አካልን እንጂ የውስጡን ማንነት አይነደፍም። ውጫዊ አካሉ በገሃዱ ዓለም ነውና ያለው በውጣ ውረድ ውስጥ ሊጎዳ ይችላል ነገር ግን እኛ ክርስቲያኖች የያዝነውን ይዘናልና በውስጣችን በሚኖረው በእርሱ በክርስቶስ ኢየሱስ ብርታት የተነሳ ለምንም ነገር ዝግጁ መሆን አለብን። በውስጣችን ኋይልን ባስቀመጠው በእርሱ በኢየሱስ ክርስቶስ ለነገሮች ሁሉ ኋይልን ተላብሰናለና፣ ጥንካሬን አስታጥቆናልና፣ ብቃትን ተጎናፅፈናልና የመጣውን ተቀብለን ለመኖር ዝግጁ ልንሆን ያስፈልጋል። ባልተሳካ ወይም ባልሆነ ጉዳይ ተይዘን መባዘን የለብንም። ለእኛ ያለው መልካም ነገሮች ሁሉ የቱንም ያህል ፈተና ቢበዛበት ከመሆን የሚከለክለው የለምና ባለመረበሽ እንጠብቀው። መጠበቅ በራሱ በክረስቶስ የሚገኝ ኋይል ነውና።
ለዛሬ አበቃሁ። ለሊታችሁ በጌታችን በመድሃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ይባረክ። መልካሙን ከእርሱ ብቻ የሆነውን የምታዩበት የያዕቆብ ለሊት ይሁንላችሁ። አሜን
ምሕረትና ሰላም ፍቅርም ይብዛላችሁ። (ይሁ 1፥2)
ባህድ ፍም
እንደ መጽሐፍ ቅዱስ እውነታ እግዚአብሔር የሚመለከውና የሚሰገድለት በመንፈስና በእውነት ነው እርሱም እንደነዚህ ያለውና ይሻልና ተብሎ እንደተፃፈ (ዮሐ 4፥23-24)። እርሱን የሚያመልክ ቢኖር ከዚህ እውነት ውጪ መሆን አይችልም። መንፈሰ ነውና ያለ ገደብና መወሰን ይመለካል፣ እውነት ነውና ከልብ በሆነ እምነትና መታዘዝ በተግባር ይመለካል። አምልኮ ለአንድ ጌታ ብቻ የተገዛ ባሪያ ሊያቀርበው የሚገባ ፍጹምና ሁለንተናዊ መገዛት ነው። አምልኮ፣ ስግደትን፣ ውዳሴን፣ አክብሮትን ዝማሬን፣ ፀሎትን፣ መስዋዕትን፣ መልካም ስራን፣ ፈሪሃ እግዚአብሔርን፣ ፍቅርን፣ ሕይወትን አጠቃሎ ለእግዚአብሔር አምላክ ብቻ መስጠት ማለት ነው። ስለዚህ አምልኮ ለአምላክህ ብቻ የሚገባና የሚሰጥ መገዛት ወይም ሁለንተናዊ ራስን መስጠት ማለት ነው።
እግዚአብሔርን እንደምንፈልገው ማምለክ አንችልም። እርሱ በሰጠን የአምልኮ መስፈርት ልናመልከው ነው ቃሉ የሚያዘው። አምልኮ ማለት አምላክ ለሆነ ብቻ መገዛት ማለት ነውና ከምናቀርበው የምስጋና መስዋህት ጀምሮ ለእግዚአብሔር መገዛት ፣ እርሱ እንደሚፈልገው ማምለክ ማለት ነው።
እግዚአብሔርን ስናመልክ እውነተኛነቱን መመዘን ያለብን የሁለንተናችን መለኪያ ወይም ቱንቢ በሆነው በሕያው ቃሉ መሰረት ነው። አምልኮ በብዙ መንገድ ይገለፃል በቃላት ሊሆን ይችላል ወይም በድርጊት ነገር ግን ዋናው ልናስተውለው የሚገባው ነገር ቢኖር የምናቀርበው አምልኮ ተመላኪው አምላክ ዘንድ ተቀባይነት ማግኘቱ ላያና ደስ መሰኘቱ ላይ ነው። እኛን ያሰደሰተን ሁሉ እግዚአብሔርን አያስደስተውም። የደስታችን ምንጭ እርሱ ነውና። የእኛ ደስታ የሚመጣው የእርሱን ደስታ ተከትሎ ነው። እኛን ደስ ብሎን እርሱ እውቅና ያልሰጠው አምልኮ ከንቱ ነው። የራሳችንን ደስታ ፍለጋ የሚደረግ አምልኮ ሊኖረን አይገባም። ካላላበን እና ሞቅ ያለ ዝማሬ ተዘምሮ እንጀታችን ካልራሰ፣ አዋራው ካልጨሰ፣ ጅማታችን እስኪታጠፍና አመዳም እስክንመስል ድረስ ካልተራብን ያልፆምን የሚመስለን፣ የሚያምርብንን ልብስ ካለበስን የማንሰማ ከመሰለን፣ ዘማሪያንና ሰባኪያን ወይም ሌሎች ካልተገኙ በእግዚአብሔር ዘንድ እውቅና የማናገኝ መስሎን ከተሰማን አምልኳችንን መፈተሽ/መመርመር ይኖርብናል።
የሰው ነገር አንጨምር:-
እግዚአብሔር በቃሉ በኩል ከነገረን የአምልኮ ስርዓት ውጪ አንዳች ነገር መጨመር እርሱን አያስደስትም። አምልኮ ላይ ያለው ትልቁ ችግር እግዚአብሔር ደስ እንዲለው የምንፈልገው የእኛን ደስ መሰኘት ተከትሎ ነው። እንዲህ ካለ ደስ መሰኘት ኋያሉ አምላክ በቸርነቱ ያውጣን።
እንኳን አይደለም በዚህ በክርስቶስ የፀጋ ዘመን/አዲስ ኪዳን በአሮጌው ብሉይ ኪዳን ዘመን እግዚአብሔር ካዘዘው ውጪ ያለ አምልኮ በእርሱ ዘንድ ከንቱ ከመሆኑ ባሻገር ቁጣን ያመጣል።
<< የአሮንም ልጆች ናዳብና አብዩድ በየራሳቸው ጥናውን ወስደው እሳት አደረጉበት፥ በላዩም ዕጣን አኖሩበት፥ በእግዚአብሔርም ፊት እርሱ ያላዘዛቸውን ሌላ እሳት አቀረቡ። እሳትም ከእግዚአብሔር ፊት ወጥቶ በላቸው፥ በእግዚአብሔርም ፊት ሞቱ። >>
ዘሌዋ 10፥1-2
እሳቱን በተመለከተ ለእግዚአብሔር መሥዋት ከሚቀርብበት መሰዊያ አይደለም የአሮን ልጆች ያመጡት። ቅዱሱ መጽሐፍ የአሮን ልጆች እሳቱን ማምጣት የነበረባቸውን ሲነግረን
<< እሳቱም በመሠዊያው ላይ ዘወትር ይነድዳል፥ አይጠፋም፤ ካህኑም ማለዳ ማለዳ እንጨት ያቃጥልበታል፤ የሚቃጠለውንም መሥዋዕት በዚያ ላይ ይረበርባል፤ በዚያም የደኅንነትን መሥዋዕት ስብ ያቃጥላል። >>
ዘሌዋ 6፥12
<< በእግዚአብሔርም ፊት ካለው መሠዊያ ላይ የእሳት ፍም አምጥቶ ጥናውን ይሞላል፥ >>
ዘሌዋ 16፥12
እርሱ ካዘዘው ዘወትር በፊቱ ከሚነደው ለክርስቶስ ኢየሱስ አምሳል ከሆነው ከመሰዊያው እሳት ውጪ ሌላ እሳት ከመንደር (ከሰፈር) ሰው ሲበርደው ወይም ምግብ ሊያበስልበት ካቀጣጠለው ከመንደር አምጥተው ጨመሩ። ይህ የሚያሳየው በእግዚአብሔር ፊት ዘወትር መንደድ የነበረበት እሳት እንደጠፋ ነው። ይህ ደግሞ በአጭር ቃል እግዚአብሔርን ደስ አላሰኘም። በፊቱ ያልነበረ እሳት በመጨመራቸው የእግዚአብሔር የቁጣ እሳት ናዳብንና አብዮድን በላቸው።
የኣሪት ዘሌዋውያን መጽሐፍ የሚያተኩረው ወይም በተደጋጋሚ የሚያወራው ለእግዚአብሔር የሚቀርብ የተወደደ የመሓዛ ሽታ ያለው የሚቃጠል መሥዋት ነው። (ዘሌዋ 1፥13/17) ይህም ጣፋጭ ሽታ ለክርስቶስ ምሳሌ እንደሆነ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በኤፌሶን መልእክቱ በምዕራፍ 5 በቁጥር 2 ላይ እንዲህ ይገልፀዋል።
<< ክርስቶስም ደግሞ እንደ ወደዳችሁ ለእግዚአብሔርም የመዓዛ ሽታ የሚሆንን መባንና መሥዋዕትን አድርጎ ስለ እናንተ ራሱን አሳልፎ እንደ ሰጠ >>
ስለዚህ ተወዳጆች ሆይ እግዚአብሔርን ማምለክ እግዚአብሔር ራሱ በፈቀደልን መንገድ እንጂ እንደ እኛ የስጋ ምኞትና መሻት አይደለም። የክርስቶስ ኢየሱስም የሆኑቱ ሥጋን ከክፉ መሻቱና ከምኞቱ ጋር ሰቀሉ ተብሎ እንደተፃፈ (ገላ 5፥24) ከዚህ እውነት ራሳችንን ከሰቀልንበት ከጌታ መስቀል ያወረደና ለሰጋዊ ምኞትና ፍላጎት ራሱን ያመቻቸ አምላኪ አሁን እንደ አሮን ልጆች እንደ ናዳብና አብዮድ እሳት አይበላቸው ይሆናል ምክንያቱም ያለንበት ዘመን በጌታ ኢየሱስ የፀጋ ዘመን ነውና ነገር ግን ከፊት የሚጠብቀው የዘላለም እሳት አለ።
ለክርስቶስ አምሳሉና ጥላ ለሆነ አግልግሎት የመጣው ቁጣ በእሳት መበላት ከሆነ ለአካሉ እግዚአብሔር ደስ የተሰኘበት የመለኮትን ቁጣ ያበረደ እንደ አቤል ያላይደለ ዘወትር የሚያስምር ክቡር ደሙን ያፈሰሰው የተወደደ የዘላለም የመሓዛ ሽታ ኢየሱስ ላይ የሚረግ ጭማሪም ሆነ እግዚአብሔር ካዘዘው ሌላ አምልኮ መፈፀም ምን ያህል ቁጣው የበረታ ይሆን???
አብ እንደዚህ ያለውን ይሻል ካለ መፅሐፉ አለ ነው ከዚህ ውጪ የሚሻው የለምና። ከመሰዊያውም ሆነ ከመንደር ፍም አምጥቶ ቢቀላቀል ውጤቱ ያው ነው ምክንያቱም ከታዘዘው ውጪ ሆኗልና። በተቀደሰና ባልተቀደሰ ነገር በሚገኝ ውህደት እግዚአብሔር አይመለክም። ከተፃፈው ውጪ ያለ አምልኮ በእግዚአብሔር ፊት ቁጣን ያመጣል። ክርስቶስ ደግሞ ከእግዚአብሔር ሊመጣብን የነበረውና ቁጣንና ፍርድ ስለ ኋጢአት መክፈል ያለበትን ዋጋ ሁሉ ከፍሏልና በእያንዳንዳችን ፈንታ ሆኖ ሊመጣ የነበረውን ቁጣ ሁሉ በእርሱ ላይ አኑሯል። ከዚህ በላይ ለእግዚአብሔር የተወደደ የመሓዛ ሽታ የለም። እግዚአብሔርን ስናመልክ ቃሉን በመጠንቀቅና በማስተዋል እንደ ቃሉ መሆን ግድ ይሏል
<< እግዚአብሔር አብን በእርሱ እያመሰገናችሁ፥ በቃል ቢሆን ወይም በሥራ የምታደርጉትን ሁሉ በጌታ በኢየሱስ ስም አድርጉት። >>
ቆላ 3፥17
በጣም የሚገርመኝ የእግዚአብሔር ቃል እንኳ በሕይወት እያለን አይደለም ማንቀላፋታችን እንኳ በኢየሱስ ክርስቶስ እንደሆነ 1ኛ ቆሮ 15፥20 ይናገራል። ታዲያ በሕይወት እያለን እስክናቀላፋ እግዚአብሔር በእኛ ላይ ያለው ፍላጎትና ዓላማ ዋጋ አውጥቶ በገዛንና የራሱ ባደረገን በናዝሬቱ ኢየሱስ ክርስቶስ ስም እርሱን ማምለክ ነው። አሜን።
Thursday, 7 November 2019
አጥንት የሌለው ሥጋ
የሰው ልጅ ሲፈጠር ጀምሮ በተለየ መልኩ የተበጀ የለም ሁላችንም በአንድ መንገድ ወደዚች ምድር የመጣን ነን። መፅሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል (ሐዋ 17፥26) እግዚአብሔር በምድር ሁሉ ላይ እንዲኖሩ የሰውን ወገኖች ሁሉ ከአንድ ፈጠረ። ስለዚህ አንድ ብሔር ከየትኞቹም ዘሮች የተውጣጣ ቢሆንም ሁሉም የአዳም ዘር ናቸው።
ታዲያ ከዚህ ድርግም ያለ እውነት የወጣ የትኛውም አስተሳሰብ ልክ አይደለም ሆኖም አያውቅም። ልዩነት የለምና የእከሌስ ዘር ብልጫው ምንድነው? የሚለውን የሚመልስ እንድስኳ የለም አይኖርምም። ሰው ከሰውነቱ የሚወድቀው በስጋ ሲያስብ ነው። ለዚህም መፅሐፍ ቅዱሳችን ይመሰክርልናል
ስለ ሥጋ ማሰብ ሞት ነውና፥ ስለ መንፈስ ማሰብ ግን ሕይወትና ሰላም ነው። ስለ ሥጋ ማሰብ በእግዚአብሔር ዘንድ ጥል ነውና፤ ለእግዚአብሔር ሕግ አይገዛምና፥ መገዛትም ተስኖታል (ሮሜ 8፥6-7)።
የእግዚአብሔር ቃል በወተትና በአጥንት ይመሰላል። ህፃን ልጅ ወተት የሚጠጣው አጥንቱ እንዲያድግ ነው። አጥንት ደግሞ ለሰው ልጅ ቆሞ ለመሄድ ዋናውን ሚና እንደሚጫወት እንዲሁ የእግዚአብሔር ቃልም በዘላለም ሕይወት ለመኖር ምርጫ የሌለበት ብቸኛ ምርጫ ነው። ከላይ ያነበብነው ቃል እንደሚነግረን ስለ መንፈስ ማሰብ ነው አጥንት የሚሆነን።
እንደው በአጭሩ ንገረኝ ካላችሁኝ ........
በስጋ ስለ ስጋ የሚያስቡ ሰዎች በዝተዋልና እያየን ያለነው አጥንት የሌላቸው ሰዎችን ነው። ሰው በዘር ሲያስብ አጥንት የሌለው በኪሎ እንደሚመዘን ጥሬ ስጋ ነው። እንደው ክምር ያለ መቆም የማይችል የተዘረገፈ ጥሬ ስጋ። የሰው ልጅ አጥንት ስላለው ነው ሰጋ የለበሰው።
ልብ በሉ እግዚአብሔር ሔዋንን ሲያበጅ አጥንትን እንጂ ስጋን ከአዳም አልወሰደም። " እግዚአብሔር አምላክም በአዳም ከባድ እንቅልፍን ጣለበት፥ አንቀላፋም፤ ከጎኑም አንዲት አጥንትን ወስዶ ስፍራውን በሥጋ ዘጋው። " (ዘፍ 2፥21) እናም በዘር የምታስቡ የአጥንታችሁ ዘር ምንድነው? ከየትኛው የአጥንት ዘር ናችሁ? መልሱልኝ?
ለካ ሰው ቆሞ የሚሄደው አጥንት ስላለው ነው እንጂ በደምና ስጋው አይደለም።
ኢትዮጵያዬ ልጆችሽን በዘር የለየ ክፋ፤ ኃይልና ስልጣን ባለው በጌታችን በመድሃኒታችን በክርስቶስ ኢየሱስ ስም የተመታ ይሁን። ዙሪያሽን የከበበው በአራቱም አቅጣጫ ያለ በየማዕዘኖችሽ ላይ ቆሞ ያደባብሽ የአባቴ የእግዚአብሔር የቁጣ እሳት ይብላው።
ልዩነቱ ጠፍቶ አንድነት በዝቶ ዓለም ሳይሆን ከሰላም ባለቤት ከሰላም አለቃ ከዓለሙ ቤዛ ሰላምሽ እንዲበዛ ለምወዳድሽ ሀገር ለእምዬ ኢትዮጵያ ይሁን !!!
ሥጋ የለበሰ ሁሉ
ይህም የሕግን ሥራ በመሥራት ሥጋ የለበሰ ሁሉ በእርሱ ፊት ስለማይጸድቅ ነው፤ ኃጢአት በሕግ ይታወቃልና። አሁን ግን በሕግና በነቢያት የተመሰከረለት የእግዚአብሔር ጽድቅ ያለ ሕግ ተገልጦአል (ሮሜ 3፥20-21)
በዚህ ቃል '' ሁሉ '' የሚለውን ቃል ከሰው ልጅ ፍጥረት ጀምሮ እስከ አሁን የምንኖረውን እንዲሁም ወደ ፊት የሚኖሩትንም የሰው ልጅን በሙሉ ያካተተ ነው። ታዲያ ይህ '' ሁሉ '' የሚለው ቃል ምንም እንኳን ሁለት ፊደል ቢሆንም ይህን ያህል ሰው በመወከሉ ከባድ ሀይለ ቃል ነው ማለት ማጋነን አይደለም።
ሥጋም የለበሰ ሁሉ የእግዚአብሔርን ማዳን ይይ ተብሎ እንደ ተጻፈ (ሉቃ 3፥3-6) ይህ በ''ሁሉ'' የተጠቀለለው ሥጋ ለባሽ ያለው ብቸኛ መዳኛ እግዚአብሔር ያዘጋጀው መንገድ ነው። ለዚህም መፅሐፍ ቅዱሳችን ሲናገር
" ነገር ግን ሰው በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን እንዲጸድቅ እንጂ በሕግ ሥራ እንዳይሆን አውቀን፥ ሥጋን የለበሰ ሁሉ በሕግ ሥራ ስለማይጸድቅ፥ እኛ ራሳችን በሕግ ሥራ ሳይሆን በክርስቶስ እምነት እንጸድቅ ዘንድ በክርስቶስ ኢየሱስ አምነናል። " (ገላ 2፥16) ይላል።
በመሆኑም ሥጋ ለባሽ ሆኖ በሕግ ሥራ (በሥራ) እጸድቃለው ብሎ ደፋ ቀና ቁጭ ብድግ የሚል ካለ ራሱን እንደ ሰው ማየት የተሳነው ብቻ ነው። እናም
ወገን ስማ
ባትሰማኝም ስማ
ባትወደውም ስማ
ባትፈልግም ስማ
ላልሰማም አሰማ
ዝም ብለህ አታቅማማ
በሆነው ባልሆነው ትግል አትግጠማ
በሥራ አትድንማ
እኮ በምን ሥራህ እረ ዘርዝርማ
ተው...ተው... ተው እንዳትሞክረው
ጭራሽ አታስበው
ላያድንህ ከሞት
ላያስጥልህ ከእሳት
ላያስገኝ ልጅነት
ላይኖርህ ነፃነት
ላያወጣ አርነት
ላይሆንልህ ሕይወት
ላይሰማህ እረፍት
የድንግዝግዝ ልፋት
የማትመካበት
አንተ የምታፍርበት
አንቺ የምታፍሪበት
አያድንም ከሞት
.
.
.
እኔም ዛሬ ፃፍኩት
" ሥጋን የለበሰ ሁሉ በእግዚአብሔር ፊት እንዳይመካ። " (1ኛ ቆሮ 1፥29)
Monday, 14 October 2019
የምኖርበት ኑሮ ይበቃኛል
የምኖርበት ኑሮ ይበቃኛል
<< ይህን ስል ስለ ጉድለት አልልም፤ የምኖርበት ኑሮ ይበቃኛል ማለትን ተምሬአለሁና። መዋረድንም አውቃለሁ መብዛትንም አውቃለሁ፤ በእያንዳንዱ ነገር በነገርም ሁሉ መጥገብንና መራብንም መብዛትንና መጉደልን ተምሬአለሁ። >> (ፊልጵ 4፥11-12)
ይህን ሲል ሐዋርያው ሁሉ ነገር ቢኖረው እንደማይጨመርለት ምንም ባይኖረው አንዳች እንደማይቀንስበት ከማወቅ ባለፈ ተምሯል። እርሱ በብልፅግና እንደማይበረታ በድህነት እንደማይደክም ተረድቷል። መማር ከማወቅ ያልፋል፣ ስለ ክርስቶስ ኢየሱስ ማወቅና ክርስቶስ ኢየሱስን ማወቅ ልዩነት እንዳላቸው መቼም ግልፅ ነው። ስለ ክርስቶስ የሰማና የተረዳ አንድ አይደለም። አብዛኛው ሰው ስለ ጌታ ብዙ የሰማ ግን ጥቂት እንኳ መማር ወይም መረዳት ያልቻለ ነው። መማር የሌለበት መስማት ጥቅም የሌለው ከንቱ ድካም ነው።
መማር ማለት የተነገረውን ቃል ተግባራዊ ለማድረግ እርምጃ መውሰድ ማለት ነው። ሐዋርያው ተምሬአለው ሲል በኑሮ በተግባር ያለፈበት እንጂ ከእውቀት አንፃር አይደለም። ሞቶ የነበረው ሕያውም የሆነው ፊተኛውና መጨረሻው አልፋ ኣሜጋ መድሃኒዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ በራእይ ዮሐንስ በምዕራፍ 2 በቁጥር 9 ላይ ዮሐንስን ለሰምርኔስ ቤተክርስቲያን እንዲፅፍ በራእይ እንደነገረው
<< መከራህንና ድህነትህን አውቃለው >>
እንደ ጌታ ኢየሱስ መከራን በመቀበል በድህነት ውስጥም ያለፈ ማንም የለም። ጌታ ይህን ጉዳይህን አውቃለው ሲል በዛ ነገር ውስጥ በሕይወት ማለፉንም ጭምር እንጂ በእውቀት ደረጃ ብቻ አይደለም። (ዕብ 2፥18, ዕብ 13፥12, 1ኛ ጴጥ 4፥1-2, ፊሊጵ 2፥7, 2ኛ ቆሮ 8፥9) መማር በመተግበር የሚገለፅ አልፈነው የምናወራው እንጂ ሰምተነው የምንገነዘበው አይደለም።
<<የምኖርበት ኑሮ ይበቃኛል>> ብዙ ጊዜ እንሰማዋለን ነገር ግን ተግባር ላይ ሲመጣ ግን ጭራሽ ትዝም የማይለን ብዙዎች ነን። ክርሰትና ከባድ የሚሆንብንም ቃሉን በሰማነው ልክ በሕይወታችን ተግባራዊ ስለማናደርገው ነው። እንደኔ እንደኔ ትልቁ የክርስቲያን ፈተና በኑሮአችን የሚገጥመንን ፈተና በቃሉ ያለመመዘን ችግር ነው። <<የምኖርበት ኑሮ ይበቃኛል>> የሚለው ቃል ለሁሉም ክርስቲያን አዲስ አይደለም ነገር ግን ተግባር ላይ ብዙዎቻችን የምንፈተንበት ጉዳይ ነው። ሰው መስራት አለበት በሰራውም ደግሞ መጠን ማግኘት አለበት እዚህ ላይ ጥያቄ የለኝም ነገር ግን የሰው ልጅ በኑሮ ከሚያገኘው ሀብት ንብረት በጨመረ ቁጥር አለመርካቱም ባገኘው መጠን እየጨመረ መሄድ የለበትም። የምንፈልገው ከሚያስፈልገን ካለፈ አደጋ ይሆንብናል።
ተወዳጆች ባለን ነገር ረክተን ተጨማሪ ለማግኘት መስራት እጅግ መልካም ነው። ብዙ ኖሮን ምኞታችን ግን ከበለጠ ወይም ካመዘነ <<የምኖርበት ኑሮ ይበቃኛል>> እንዴት ማለት እንችላለን? ያለን ከበቂ በላይ ሆኖ ሳለ መስገብገብ ያለንን ያሳጣል ምክንያቱም የምኞት ክፋቱ ባለን ነገር እንዴት መጠቀም እንዳለብን እንኳ እንዳንችል አርጎ ያሳውራልና።
ለኑሮ የሚያስፈልገን ምን ያህል እንደሆነ ካላወቅን ባለን ነገር አጣጥመን መጠቀም አንችልም። ያለንን ነገር እንኳን ለሰው ለራሳችን እንኳ በማይጠቅም መልኩ እናባክነዋለን። ስለዚህ ያለንን እንወቅ ባለንም እንርካ ያን ጊዜ ያለንን እንደሚበቃን እናውቃለን። ከሁሉም በላይ ደግሞ የእውነተኛ እርካታ ምንጭ ጌታ ኢየሱስ አለን። እንስራ አስትቶ ደስታ የሚሞላ አንዳችን የሌለን ስንሆን ሁሉ እኛ ሆኗል የሚያስብል ጌታ ይባረክ። እርሱ ብቻ እስከ ዘላለም ከበቂ በላይ ነው።
<< ይህን ስል ስለ ጉድለት አልልም፤ የምኖርበት ኑሮ ይበቃኛል ማለትን ተምሬአለሁና። መዋረድንም አውቃለሁ መብዛትንም አውቃለሁ፤ በእያንዳንዱ ነገር በነገርም ሁሉ መጥገብንና መራብንም መብዛትንና መጉደልን ተምሬአለሁ። >> (ፊልጵ 4፥11-12)
ይህን ሲል ሐዋርያው ሁሉ ነገር ቢኖረው እንደማይጨመርለት ምንም ባይኖረው አንዳች እንደማይቀንስበት ከማወቅ ባለፈ ተምሯል። እርሱ በብልፅግና እንደማይበረታ በድህነት እንደማይደክም ተረድቷል። መማር ከማወቅ ያልፋል፣ ስለ ክርስቶስ ኢየሱስ ማወቅና ክርስቶስ ኢየሱስን ማወቅ ልዩነት እንዳላቸው መቼም ግልፅ ነው። ስለ ክርስቶስ የሰማና የተረዳ አንድ አይደለም። አብዛኛው ሰው ስለ ጌታ ብዙ የሰማ ግን ጥቂት እንኳ መማር ወይም መረዳት ያልቻለ ነው። መማር የሌለበት መስማት ጥቅም የሌለው ከንቱ ድካም ነው።
መማር ማለት የተነገረውን ቃል ተግባራዊ ለማድረግ እርምጃ መውሰድ ማለት ነው። ሐዋርያው ተምሬአለው ሲል በኑሮ በተግባር ያለፈበት እንጂ ከእውቀት አንፃር አይደለም። ሞቶ የነበረው ሕያውም የሆነው ፊተኛውና መጨረሻው አልፋ ኣሜጋ መድሃኒዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ በራእይ ዮሐንስ በምዕራፍ 2 በቁጥር 9 ላይ ዮሐንስን ለሰምርኔስ ቤተክርስቲያን እንዲፅፍ በራእይ እንደነገረው
<< መከራህንና ድህነትህን አውቃለው >>
እንደ ጌታ ኢየሱስ መከራን በመቀበል በድህነት ውስጥም ያለፈ ማንም የለም። ጌታ ይህን ጉዳይህን አውቃለው ሲል በዛ ነገር ውስጥ በሕይወት ማለፉንም ጭምር እንጂ በእውቀት ደረጃ ብቻ አይደለም። (ዕብ 2፥18, ዕብ 13፥12, 1ኛ ጴጥ 4፥1-2, ፊሊጵ 2፥7, 2ኛ ቆሮ 8፥9) መማር በመተግበር የሚገለፅ አልፈነው የምናወራው እንጂ ሰምተነው የምንገነዘበው አይደለም።
<<የምኖርበት ኑሮ ይበቃኛል>> ብዙ ጊዜ እንሰማዋለን ነገር ግን ተግባር ላይ ሲመጣ ግን ጭራሽ ትዝም የማይለን ብዙዎች ነን። ክርሰትና ከባድ የሚሆንብንም ቃሉን በሰማነው ልክ በሕይወታችን ተግባራዊ ስለማናደርገው ነው። እንደኔ እንደኔ ትልቁ የክርስቲያን ፈተና በኑሮአችን የሚገጥመንን ፈተና በቃሉ ያለመመዘን ችግር ነው። <<የምኖርበት ኑሮ ይበቃኛል>> የሚለው ቃል ለሁሉም ክርስቲያን አዲስ አይደለም ነገር ግን ተግባር ላይ ብዙዎቻችን የምንፈተንበት ጉዳይ ነው። ሰው መስራት አለበት በሰራውም ደግሞ መጠን ማግኘት አለበት እዚህ ላይ ጥያቄ የለኝም ነገር ግን የሰው ልጅ በኑሮ ከሚያገኘው ሀብት ንብረት በጨመረ ቁጥር አለመርካቱም ባገኘው መጠን እየጨመረ መሄድ የለበትም። የምንፈልገው ከሚያስፈልገን ካለፈ አደጋ ይሆንብናል።
ተወዳጆች ባለን ነገር ረክተን ተጨማሪ ለማግኘት መስራት እጅግ መልካም ነው። ብዙ ኖሮን ምኞታችን ግን ከበለጠ ወይም ካመዘነ <<የምኖርበት ኑሮ ይበቃኛል>> እንዴት ማለት እንችላለን? ያለን ከበቂ በላይ ሆኖ ሳለ መስገብገብ ያለንን ያሳጣል ምክንያቱም የምኞት ክፋቱ ባለን ነገር እንዴት መጠቀም እንዳለብን እንኳ እንዳንችል አርጎ ያሳውራልና።
ለኑሮ የሚያስፈልገን ምን ያህል እንደሆነ ካላወቅን ባለን ነገር አጣጥመን መጠቀም አንችልም። ያለንን ነገር እንኳን ለሰው ለራሳችን እንኳ በማይጠቅም መልኩ እናባክነዋለን። ስለዚህ ያለንን እንወቅ ባለንም እንርካ ያን ጊዜ ያለንን እንደሚበቃን እናውቃለን። ከሁሉም በላይ ደግሞ የእውነተኛ እርካታ ምንጭ ጌታ ኢየሱስ አለን። እንስራ አስትቶ ደስታ የሚሞላ አንዳችን የሌለን ስንሆን ሁሉ እኛ ሆኗል የሚያስብል ጌታ ይባረክ። እርሱ ብቻ እስከ ዘላለም ከበቂ በላይ ነው።
Tuesday, 17 September 2019
ታላቅ መዳን
ሰው ከብዙ ነገር ሊድን ይችላል ነገር ግን በመፅሐፍ ቅዱሳችን እንደምናነበው ዘላለማዊ መዳንን የሚያክል ታላቅ መዳን የለም። ይህ መዳን አጠቃላይ የክርስትናን እምነት ማዕከል ያደረገና ከሞት ወደ ዘላለማዊ የሕይወት አቅጣጫ ያሻገረም ጉዳይ ነው። ታላቅነቱም በጊዜ የተገደበ ስላልሆነ (ህያው በመሆኑ) እና ራሱ እግዚአብሔር ለሰው ልጅ የሰጠው ወይም ያደረገው ምህረት በመሆኑ ታላቅ አሰኝቶታል።
የሰው ልጅ ይህ ታላቅ መዳን ለምን አስፈለገው? ያሉ እንደሆነ:- መፅሐፍ ቅዱስ ሲናገር ሰው ሁሉ ኋጢአተኛ እንደሆነ ነው። ኋጢአተኝነቱም የመጣው በአዳም ኋጢአተኛ ማንነት ስለተወለድን እንደ ሆነ ሮሜ 5፥12 ይናገራል። ስለሆነም አዳም እግዚአብሔር ያዘዘውን ትዕዛዝ በተላለፈ ጊዜ ኋጢአት ወደ ዓለም ከመግባቱም ባሻገር ባለመታዘዝ ጠንቅ እግዚአብሔር የፈረደው የሞት ፍርድ ለሰው ሁሉ ሊደርስ ችሏል። እስኪ ሰለ ሰው ኋጢአተኝነት መፅሐፍ ቅዱስ ምን ይላል የሚለውን በጥቂቱ ተመልከቱ:-
ብሉይ (አሮጌው) ኪዳን
=}} "ሁላችን እንደ ርኩስ ሰው ሆነናል፥ ጽድቃችንም ሁሉ እንደ መርገም ጨርቅ ነው፤ ሁላችንም እንደ ቅጠል ረግፈናል፥ በደላችንም እንደ ነፋስ ወስዶናል። " (ኢሳ 64፥6)
=}} "ሁሉ ዐመፁ በአንድነትም ረከሱ በጎ ነገርን የሚሠራ የለም፤ አንድም ስንኳ የለም። " (መዝ 14፥3)
አዲስ ኪዳን
=}} "ሁሉ ኃጢአትን ሠርተዋልና የእግዚአብሔርም ክብር ጎድሎአቸዋል " (ሮሜ 3፥23)
=}} '' ጻድቅ የለም አንድ ስንኳ፤ አስተዋይም የለም፤ እግዚአብሔርንም የሚፈልግ የለም፤ ሁሉ ተሳስተዋል፥ (ሮሜ 3፥11-12)
በአንድነትም የማይጠቅሙ ሆነዋል፤ ቸርነት የሚያደርግ የለም፥ አንድ ስንኳ የለም። ''
በነዚህ የመፅሐፍ ቅዱስ ንባቦች መሰረት የሰው ዘር በሙሉ በኋጢአት ውስጥ እንደሆነና በራሱ ኋጢአት ከሚያስከትለው የሞት ፍርድ (ሮሜ 6፥23 የኋጢአት ደሞዝ ሞት ነው) ሊያድን ባለመቻሉ የእግዚአብሔር ማዳን አስፈልጎታል። የሰው ዘር በአጠቃላይ ከፀሐይ መውጫ እስከ መጥለቂያው ያለን ሰው ሁሉ ከነበረበት መሰረታዊ ችግር እንዲድን በምህረቱ ብዛት ባለጠጋ የሆነው አባታችን እግዚአብሔር አንድ የመዳን መንገድ አዘጋጀ እርሱም አንድያ ልጁ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። (ዮሐ 14፥6)
ኢየሱስ
ከስሙ ትርጉም ብንነሳ ኢየሱስ ማለት ሕዝቡን ከኋጢአታቸው የሚያድን ማለት ነው (ማቴ 1፥23)። ኢየሱስ የአባቱን ፈቃድ በመታዘዝ እስከ ሞት ድረስ ዋጋ በመክፈል የሰውን ልጅ ከነበረበት ኩነኔ ነፃ አድርጎአል። እስኪ እነዚህ የመፅሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች አንብቡ
" የሰው ልጅ የጠፋውን ሊፈልግና ሊያድን መጥቶአለና"
(ሉቃ19፥10) " በነገው ዮሐንስ ኢየሱስን ወደ እርሱ ሲመጣ አይቶ እንዲህ አለ። እነሆ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ" (ዮሐ 1፥29) " ኃጢአተኞችን ሊያድን ክርስቶስ ኢየሱስ ወደ ዓለም መጣ የሚለው ቃል የታመነና ሁሉ እንዲቀበሉት የተገባ ነው " (1ኛጢሞ1፥15) " ለኃጢአት ሞተን ለጽድቅ እንድንኖር፥ እርሱ ራሱ በሥጋው ኃጢአታችንን በእንጨት ላይ ተሸከመ " (1ኛ ጴጥ 2፥24)
እነዚህ ጥቅሶች ኢየሱስ ክርስቶስ የሰውን ዘር በሙሉ የማዳን ዓላማ ይዞ ከሰማይ እንደመጣ ያሳያሉ። በመሆኑም እርሱ ኋጢአት ስለሌለበት ስለእኛ መሞትና ከኋጢአታችንም ማዳን ተችሎታል። ይህን የማዳን ስራ በሰማይም ሆነ በምድር ከጌታችን ከመድሃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ በቀር የተቻለውም የሚቻለውም የለም። የእግዚአብሔር ቃል በሐዋርያት ሥራ 4: 12 ተፅፎ እንደምናነበው "፤ መዳንም በሌላ በማንም የለም፤ እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና። "
ይህ መዳን እግዚአብሔር አባታችን እንደባለጠግነቱ መጠን እንዲያው በፀጋው ያደለን ነፃ ስጦታችን ነው። በመስራት ያላይደለ በመቀበል የሚገኝ መዳን። ለዚህም አሁንም መፅሐፍ ቅዱሳችን ያረጋግጥልናል። ነገር ግን እግዚአብሔር በምሕረቱ ባለ ጠጋ ስለ ሆነ፥ ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ በበደላችን ሙታን እንኳ በሆንን ጊዜ ከክርስቶስ ጋር ሕይወት ሰጠን፥ በጸጋ ድናችኋልና ጸጋው በእምነት አድኖአችኋልና፤ ይህም የእግዚአብሔር ስጦታ ነው እንጂ ከእናንተ አይደለም፤ ማንም እንዳይመካ ከሥራ አይደለም። (ኤፌ 2፥4-9)
እንደ ምሕረቱ መጠን ለአዲስ ልደት በሚሆነው መታጠብና በመንፈስ ቅዱስ በመታደስ አዳነን እንጂ፥ እኛ ስላደረግነው በጽድቅ ስለ ነበረው ሥራ አይደለም፤ ያን መንፈስም፥ በጸጋው ጸድቀን በዘላለም ሕይወት ተስፋ ወራሾች እንድንሆን፥ በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በእኛ ላይ አትርፎ አፈሰሰው። (ቲቶ 3፥4-7)
ኢየሱስ ከእያንዳንዳችን የጎደለብንን የእግዚአብሔር ክብር ደግሞም ከኋጢአታችን የተነሳ ተላልፎብን ከነበረው ዘላለማዊ የሞት ፍርድ (ሮሜ 6፥23) ውስጥ ለሚኖር ሁሉ ይህን የኢየሱስ ክርስቶስ ብቸኛ አዳኝነት መስማት ታላቅ የምስራች ነው።
ይህን የምታነቡ ወንድምና እህቶች የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ያደረገልንን ይህን ታላቅ መዳን ቸል ብንል ከሞት ፍርድ እንዴት እናመልጣለን? አይምሰላችሁ እንዴትም አናመልጥም። ይልቅስ ሐዋርያው ጳውሎስ ለኤፌሶን ሰዎች በፃፈው መልእከቱ ላይ " እናንተም ደግሞ የእውነትን ቃል፥ ይኸውም የመዳናችሁን ወንጌል፥ ሰምታችሁ ደግሞም በክርስቶስ አምናችሁ፥ በተስፋው መንፈስ በመንፈስ ቅዱስ ታተማችሁ " (ኤፌ 1፥13) እንዳለው ኢየሱስን የሕይወታችን መድሃኒት በማድረግና እርሱን በማመን በሚገኝ ቅድስና ቀሪውን ዘመናችሁን በእርሱ ለመኖር አሁኑኑ ይወስኑ።
ይህንንም ለማድረግ ቀጠሮ አትያዙ ለመልካም ነገር ቀጠሮ አያስፈልገውምና አሁኑኑ ወስኑ። መፅሐፍ ቅዱስ '' እነሆ የተወደደ ሰዓት አሁን ነው እነሆ የመዳንም ቀን አሁን ነው '' ይላልና (2ኛ ቆሮ 6፥2) " በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና። " (ዮሐ 3፥16) ተብሎም እንደተፃፈ እግዚአብሔር ያዘጋጀውን ዘላለማዊ መፍትሄ ልጁን ኢየሱስን በማመንና ራስህን ወይም ራስሽን በንሰሐ መንፈስ በክርስቶስ ደም በመታጠብ ብቻ ወደሚገኝ ቅድስና በመምጣት ክፉ ከሆነው ከዚህ ዓለም ድነው የዘላለም ሕይወት ያገኙ ዘንድ በፀሎት መንፈስ ይህ ተፃፈ።
Sunday, 15 September 2019
ልዩነት
ሁሉ በአዳም እንደሚሞቱ እንዲሁ ሁሉ በክርስቶስ ደግሞ ሕያዋን ይሆናሉና።
1ኛ ቆሮ 15፥22
የሰው ልጅ አስቀድሞ ሲፈጠር ዘላለማዊነትን ከእግዚአብሔር ተሰጥቶት ነበረ፡፡ ሰው ደካማ ሆኖ በመገኘቱ የፈጣሪውን ትዕዛዝ ባለመጠበቁና በማሳዘኑ የተነሳ ዘላለማዊ መሆኑን አስቋርጦ ነበረ፡፡ ቋሚ የነበረው በገዛ ስራውና እምነት በማጉደሉ በሞት ቅጣት የመኖሪያ ገደብ መጣበት፡፡
ታዲያ የሰው ልጅ ምንም እንኳ በገዛ ፈቃዱ ወዶና ፈቅዶ አምላኩን ቢበድልም እግዚአብሔር ግን በምሕረቱ ባለ ጠጋ ስለ ሆነ (ኤፌ 2÷4) የሰውን ልጅ ከፍጥረቱ በሙሉ አክብሮና አልቆ በራሱ መልክና አምሳል ስለፈጠረው የአሳቹ የዲያብሎስ ተገዥ ሆኖ እንዲቀር አልወደደምና ለትዕዛዝ ተላላፊው አዳም የመዳን ተስፋ ተሰጠው እርሱም የዓለምን ኋጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ (ዮሐ 1÷29) የናዝሬቱ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።
እግዚአብሔር እኛን ሲፈጥረን እንዳችን ከአንዳችን እንዳንመሳሰል አድርጎ ነው፡፡ ሁላችንም የየራሳችን መልክና ገጽታ እንዲኖረን አድርጎ ነው የፈጠረን፡፡ ይህ ማለት ግን እግዚአብሔር ፍትሃዊ አይደለም አያስብልም ምክንያቱም የሁላችንንም ልዩነት አንድ አካል ወደምንሆንበት ወደ ልጁ ህብረት ጠርቶናልና (1ኛ ቆሮ 1÷9) ለዚህም አንድያ ልጁን እስከማይራራ ድረስ ለሞት አሳልፎ ሰቷልና፡፡ የሰው ልጅም ትልቁ ድል በጌታ የመሆኑ ጉዳይ የሆነውም ለዚህ ነው፡፡ የቱንም ያህል የአሰተሳሰብም ሆነ߹ ሌላ ልዩነት በመካከላችን ቢኖርም በዚህ ልዩነት ውስጥ ተስማምተን በፍቅር እንድንኖር ቃሉ ይነግረናል (ሮሜ 12÷18)፡፡ ፍቅር ነውና ያዳነን፡፡
እኛ ሰዎች አብዛኛውን ጊዜ ከሌሎች ተሽለን የምንታይበትን ነገር እንፈልጋለን፡፡ ሰዎች በአትኩሮት እንዲመለከቱን ከመፈለጋችን የተነሳ እይታ ውስጥ ለመግባት ብዙ እንጥራለን ነገር ግን እግዚአብሔር እንደሚያየው ሰው አንኖርም፡፡ በሰው ፊት እንጂ በእርሱ ፊት ለመኖር አናስብም፡፡ ለምድራዊ ሕይወት ብዙ እንለፋለን የሰማያዊውን (ዘላለማዊውን) ግን በዳተኝነት እንኖራለን፡፡ ለስጋዊ ሕይወት የምንደክመውን ያህል ለመንፈሳዊ ሕይወት እምብዛም ነን፡፡ ለዚህ ነው እግዚአብሔር የሰው ልጅ የልቡ ሀሳብና ምኞት ሁልጊዜ ፈጽሞ ክፉ እንደሆነ አየ ተብሎ የተጻፈው ዘፍ 6÷5፡፡
የሰው ልጅ ውድቀት በአዳም አለመታዘዝ እንደመጣና (ዘፍ 3÷17 ) ደሞዝ የሆነውን ሞት ለትውልዱም ጭምር ደረሰበት ሮሜ 5÷12፡፡ እግዚአብሔር አምላክ ገዢ እንደመሆኑ በቃሉ በኩል እንድናደርገውና ደግሞ እንድንታቀብ የሚከለክል ትዕዛዝ አለው፡፡ ፊተኛው አዳም የተሰጠውን ትዕዛዝ በመተላለፉ በኋጢአት ሲወድቅና ሲራቆት እናነባለን። ነገር ግን ኋለኛው አዳም (ጌታ ኢየሱስ) በምስሉም እንደ ሰው ተገኝቶ ራሱን አዋረዶ ለሞትም ይኽውም የመስቀል ሞት የታዘዘ ሆነ (ፊልጵ 2÷8)፡፡
ፊተኛው አዳም በማጥፋቱ ራቁቱን ሲሆን (ዘፍ 2÷25) ኋለኛው ግን ሁላችንን ስለ ማጽደቅ ያለ ኋጢአቱ በቀራንዮ አደባባይ በመስቀል ላይ እርቃኑን ሆነ (ሉቃ 23÷34)፡፡
ፊተኛው አዳም ባለመታመኑ በእርሱ በኩል ኋጢአት በሰው ልጅ ላይ በሙሉ ነገሰ ነገር ግን ቅዱስና ጻድቅ ያለ ተንኮልና ነውር በንጽህና የኖረው ከኋጢአተኞችም የተለየ ኋለኛው አዳም በመስቀል ላይ በሰራው ስራ ነውራችንን ሸፈነ፡፡ ፊተኛው አዳም የስራውን ደሞዝ ወስዶ ለትውልዱም የክፋት ስራውን አጋራ ኋለኛው አዳም ግን ስለ በደላችን ሞቶ ስለ ጽድቃችን ከሙታን ተነሳ፡፡
በፊተኛው አዳም የሁላችንም እጣ ፈንታ ሞት ሲሆን እንደ እግዚአብሔር ያለ ይቅር ባይ የለምና በልጁ በኢየሱስ በኩል ያጣነውን የዘላለም ሕይወት መስጠት ነው (ሮሜ 6÷23)፡፡ መጽሐፍ ቅዱሳችንም ይህን በአጽንሆት ይነግረናል በፊተኛው አዳም ምክንያት እግዚአብሔር በሞት ሲቀጣን ነገር ግን በኋለኛው አዳም የዘላለም ሕይወት ሰጠን፡፡ እውተኛ አምላክ ብቻ የሆንህ አንተን የላክኽውንም ኢየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ ይህች የዘላለም ሕይወት ናት (ዮሐ 17÷3)፡፡
ውድ እንባቢያን ከሰው የምንጠብቀው አንዳች ነገር እንዳይኖር አርጎ ጌታ ኢየሱስ ጽድቅን አድርጎልናል፡፡ ከእኛ የሚጠበቀው በእግዚአብሔር ፍቃድ ላይ መመስረት ብቻ ነው እርሱም እርሱ በላከው በልጁና በሰራው ስራ ማመን ነው፡፡ ይህን መቀበል ላመነ ሰው ቀላል ነው ነገር ግን እንዴት የዚህን ያህል ይቀላል በማለት ብዙዎች ለመቀበል ተቸግረዋል፡፡ በፊተኛው አዳም የመጣውን ኩነኔ ያለማቅማማት ተቀብለው ሲኖሩ በሚበልጥ የረዳንንና ሌላ ስራ ሳያስፈልግ ዘላለም በሚያድን የኪዳን ደም የገዛንን የኢየሱስን የማዳን ስራ ግን አይቀበሉም፡፡
ቅዱስ ቃሉ በተደጋጋሚ ኢየሱስ የዘላለም ሕይወት እንደሆነ ይነግረናል ከዚህ የሚበልጥ ነገር ከየት ይምጣ?፡ ግልጽና ጥርጥር በማያስነሳ መልኩ እንዲህ ይላል እውነት እውነት እላችኋለሁ በእኔ የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፡፡ (ዮሐ 6÷47) የእግዚአብሔር ቃል ሊነግረን በፈለገው መጠን በቃሉ እንድናምን የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ የእግዚአብሔር አብ ፍቅር የመንፈስ ቅዱስም ህብረት ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን።
Thursday, 12 September 2019
ከየቤታችሁ አንፃር
ነህምያ የፈረሰውን የእስራኤልን ቅጥር ሲያድስ ከፈረሱት በሮች ውስጥ የበጉ በር ተብሎ ከሚጠራው እንደ ጀመረ መፅሐፍ ቅዱሳችን ይናገራል (መፅሐፈ ነህምያ 3፥1)። በጣም የሚደንቀው ግን የእስራኤል ቅጥር ማደስ ያለቀውም በበጉ በር ነው(መፅሐፈ ነህምያ 3፥32) ። በበጉ በር ተጀምሮ በበጉ በር ያለቀ ስራ ለእኛ ለክርስቲያኖች ትልቅ መልእክት አለው። በሕይወታችን እግዚአብሔር ዘመን ሲጨምርልን በክርስቶስ ኢየሱስ ፀጋ ተቀብለን ደግሞም በእርሱ ላይ ባለን እምነት በመፅናት መደምደም እንዳለብን ይነግረናል።
እኔን እጅግ የሚገርመኝ አንድ ነገር አለ። ነህምያ የፈረሰውን ቅጥር እንዲሰራ ከተጠቀመባቸው መንገዶች አንዱ ከየቤታችው አንፃር የነበሩትን የፈረሱትን ቅጥር ወይም በር ማደስ ነበር (መፅሐፈ ነህምያ 3፥28)። ሰው ከፊቱ የተደቀነበትን ችግር መፍታት ከቻለ የእርሱ ችግር ሌላ ሰው ጋር ጉዳት እንዳይደርስ ያደርጋል። በጨረስነው ዓመት በአእምሮዬ የሚመላለስ አቋም አለ። " የድርሻህን ተወጣ " (Play Your Part) የሚል።
ሁሉም ክርስቲያን በአገልግሎት የድርሻውን ቢወጣ ምን ያህል ለውጥ ሊያመጣ እንደሚችል ሳስብ እደነቃለው። አንዱ ከሌላው ሳይጠብቅ በራሱ ማድረግ ያለበትን ቢያደርግ ችግር የምንለውን ነገር በቀላሉ ማለፍ እንችላለን። ከአገልግሎት አንፃር ክርስቲያን የሚሞተው ከሰው የጠበቀ ቀን ነው የሚል ፅሁፍ ያነበብኩት ይህን ለማለት የፈለገ ይመስለኛል።
በዚህ ምድሪቱን በከደነው በጌታ ኢየሱስ ፀጋ የተቀበልነው 2012 ዓመተ ምህረት ጌታን በታማኝነት በማገልገል በየአንፃራችን ያለውን ድርሻችንን የምንወጣበት ዓመት እንዲሆንልንና በእርሱ ላይ ባለን እምነት እንድንፀና ፀጋው ይርዳን። ከሰው የምንጠብቅበት ሳይሆን የድርሻችንን የምንወጣበት ደግሞም ከመገልገል አልፈን የምናገለግልበትና የምንዘረጋበት ዓመት ይሁንልን።
እስራኤላዊያን በነህምያ አስተባባሪነት እያንዳንዳቸው በቤታቸው አንፃር ያለውን ቅጥር እንዳደሱ፥ እያንዳንዱም በቅጥሩ ሥራላይ ድርሻ እንዳላቸው ሁሉ ዛሬም በአዲስ ኪዳን የምንገኝ አማኞች ሁላችን ደግሞም የክርስቶስ አካልብልቶች እንደመሆናችን መጠን በ1ኛ ቆሮንጦስ በምዕራፍ 12 በቁጥር 14 - 31 ላይ እንደተገለፀው ሁላችንም በአካሉ ውስጥ እኛ ብቻ ልንወጣው ወይም ልናደርገው የተገባ ኃላፊነትና ሥራአለን። የማያስፈልግ የአካል ክፍል እንደሌለ ሁሉ የማያስፈልግ (ሥራ የሌለው) ክርስቲያን በእግዚአብሔር መንግስት ውስጥየለም። እያንዳንዳችን በአንፃራችን ያለውን የእግዚአብሔር ሥራ በትጋት እየሰራን የምንኖርበት ዘመን እንዲሆን እርሱ ይርዳን።
እንደ ነህምያበቅንዓት፥ በሙሉ መሰጠትና ቁርጠኝነት በክርስቶስ የተፈጠርንለትን መልካሙን ሥራ ለማድረግ እኛም ፈቃዳችንን ለፈቃዱበማስገዛት፥ ስለ በጎ ፈቃዱ መፈለግንም፥ ማድረግንም በእኛ የሚሰራ አምላክ በእኛ የጀመረውን መልካም ሥራእርሱ ራሱ ይፈፅመዋልና እርሱ ላይ በመደገፍ ማገልገል ይሁንልን።
የተወደደው ዓመታችን በኢየሱስ ስም ይባረከ።
እኔን እጅግ የሚገርመኝ አንድ ነገር አለ። ነህምያ የፈረሰውን ቅጥር እንዲሰራ ከተጠቀመባቸው መንገዶች አንዱ ከየቤታችው አንፃር የነበሩትን የፈረሱትን ቅጥር ወይም በር ማደስ ነበር (መፅሐፈ ነህምያ 3፥28)። ሰው ከፊቱ የተደቀነበትን ችግር መፍታት ከቻለ የእርሱ ችግር ሌላ ሰው ጋር ጉዳት እንዳይደርስ ያደርጋል። በጨረስነው ዓመት በአእምሮዬ የሚመላለስ አቋም አለ። " የድርሻህን ተወጣ " (Play Your Part) የሚል።
ሁሉም ክርስቲያን በአገልግሎት የድርሻውን ቢወጣ ምን ያህል ለውጥ ሊያመጣ እንደሚችል ሳስብ እደነቃለው። አንዱ ከሌላው ሳይጠብቅ በራሱ ማድረግ ያለበትን ቢያደርግ ችግር የምንለውን ነገር በቀላሉ ማለፍ እንችላለን። ከአገልግሎት አንፃር ክርስቲያን የሚሞተው ከሰው የጠበቀ ቀን ነው የሚል ፅሁፍ ያነበብኩት ይህን ለማለት የፈለገ ይመስለኛል።
በዚህ ምድሪቱን በከደነው በጌታ ኢየሱስ ፀጋ የተቀበልነው 2012 ዓመተ ምህረት ጌታን በታማኝነት በማገልገል በየአንፃራችን ያለውን ድርሻችንን የምንወጣበት ዓመት እንዲሆንልንና በእርሱ ላይ ባለን እምነት እንድንፀና ፀጋው ይርዳን። ከሰው የምንጠብቅበት ሳይሆን የድርሻችንን የምንወጣበት ደግሞም ከመገልገል አልፈን የምናገለግልበትና የምንዘረጋበት ዓመት ይሁንልን።
እስራኤላዊያን በነህምያ አስተባባሪነት እያንዳንዳቸው በቤታቸው አንፃር ያለውን ቅጥር እንዳደሱ፥ እያንዳንዱም በቅጥሩ ሥራላይ ድርሻ እንዳላቸው ሁሉ ዛሬም በአዲስ ኪዳን የምንገኝ አማኞች ሁላችን ደግሞም የክርስቶስ አካልብልቶች እንደመሆናችን መጠን በ1ኛ ቆሮንጦስ በምዕራፍ 12 በቁጥር 14 - 31 ላይ እንደተገለፀው ሁላችንም በአካሉ ውስጥ እኛ ብቻ ልንወጣው ወይም ልናደርገው የተገባ ኃላፊነትና ሥራአለን። የማያስፈልግ የአካል ክፍል እንደሌለ ሁሉ የማያስፈልግ (ሥራ የሌለው) ክርስቲያን በእግዚአብሔር መንግስት ውስጥየለም። እያንዳንዳችን በአንፃራችን ያለውን የእግዚአብሔር ሥራ በትጋት እየሰራን የምንኖርበት ዘመን እንዲሆን እርሱ ይርዳን።
እንደ ነህምያበቅንዓት፥ በሙሉ መሰጠትና ቁርጠኝነት በክርስቶስ የተፈጠርንለትን መልካሙን ሥራ ለማድረግ እኛም ፈቃዳችንን ለፈቃዱበማስገዛት፥ ስለ በጎ ፈቃዱ መፈለግንም፥ ማድረግንም በእኛ የሚሰራ አምላክ በእኛ የጀመረውን መልካም ሥራእርሱ ራሱ ይፈፅመዋልና እርሱ ላይ በመደገፍ ማገልገል ይሁንልን።
የተወደደው ዓመታችን በኢየሱስ ስም ይባረከ።
Thursday, 25 April 2019
መካከለኝነቱ አላበቃም።
አንድ እግዚአብሔር አለና፥ በእግዚአብሔርና በሰውም መካከል ያለው መካከለኛው ደግሞ አንድ አለ፥ እርሱም ሰው የሆነ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው፤ ራሱንም ለሁሉ ቤዛ ሰጠ፥ ይህም በገዛ ዘመኑ ምስክርነቱ ነበረ፤ (1ኛ ጢሞ 2፥5-6)
መታረቃችን በሞቱ
መዳናችን በሕይወቱ
ኢየሱስ የማዳንን ስራ አንድ ጊዜ በመስቀል ላይ ፈፅሟል ነገር ግን ዛሬም ድረስ ህያው ነው። የዛሬ 2011 ዓመት የተሰራው ስራ አሁንም ትኩስነቱ እንዳለ ነው። ከእግዚአብሔር ጋር መታረቃችን በኢየሱስ ሞት አንድ ጊዜ የተጠናቀቀና የተፈጸመ ቢሆንም መካከለኛነቱ ግን ዛሬም ድረስ ነው ወደፊትም ይኖራል።
በእርግጥ ክርስቶስ ኢየሱሰ ዛሬ ስለመታረቃችን አንዳች የሚያደርገው ስራ የለም። በሰማያት በግርማው ዙፋን ቀኝ ያለው ሊቀ ካህናችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ቀደሙት የብሉይ ካህናት ዕለት ዕለት ስለ በደልና ስለ ኃጢአት የሚሆን ማናቸውንም ዓይነት መስዋዕት አያቀርብም። ለመስቀል ሞት ራሱን አሳልፎ ሲሰጥ ይህን አንድ ጊዜ ፈጽሞ አድርጎታልና። ስለዚህ የክርስቶስ የማስታረቅ ሥራ የተጠናቀቀ ነው ማለት ነው። ይህ ማለት መካከለኝነቱ ተጠናቋል ማለት ነውን? አይደለም!!! መጽሐፍ እንዲህ ይላል
" ጠላቶች ሳለን ከእግዚአብሔር ጋር በልጁ ሞት ከታረቅን፥ ይልቁንም ከታረቅን በኋላ በሕይወቱ እንድናለን " (ሮሜ 5፥10)
መታረቃችን በሞቱ መዳናችን ግን በሕይወቱ ነው። ለመታረቃችን መካከለኛ የነበረው ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ዛሬም ለሰዎች መዳን መካከለኛ ነው።
ሐዋርያው ሲናገር ከተናገርነውም ዋና ነገሩ ይህ ነው፤ በሰማያት በግርማው ዙፋን ቀኝ የተቀመጠ እንዲህ ያለ ሊቀ ካህናት አለን፤ እርሱም የመቅደስና የእውነተኛይቱ ድንኳን አገልጋይ ነው፥ እርስዋም በሰው ሳይሆን በጌታ የተተከለች ናት። (ዕብ 8፥1-2)
በዚህ በማያልፍ ሕይወት ኃይል በመልከ ጸዲቅ ሹመት የዘላለም ሊቀ ካህን በሆነበት ሰማያዊ አገልግሎቱ ነው ሰዎች የሚድኑት። የማዳኑ ስራው ከማያልፈው ሕይወቱና በግርማው ዙፋን ቀኝ ካለው ሰማያዊ አገልግሎቱ ጋር የተወዳጀና የተቆራኘ መሆኑ ግልፅ ነው።
አሁንም ሐዋርያው በዚህ ከሰማያዊ አገልግሎቱ ጋር በተያያዘ ሲመሰክር " ስለ እነርሱም ሊያማልድ ዘወትር በሕይወት ይኖራልና ስለዚህ ደግሞ በእርሱ ወደ እግዚአብሔር የሚመጡትን ፈጽሞ ሊያድናቸው ይችላል። " (ዕብ 7፥25) ያለውም ለዚህ ነው።
ሰማይ ስሚ
ምድርም አድምጪ
ትናንት ያዳነን
ዛሬም ነገም የሚያድን ኢየሱስ ብቻ ነው።
"ኢየሱስ ክርስቶስ ትናንትና ዛሬ እስከ ለዘላለምም ያው ነው። " (ዕብ 13፥8)
Saturday, 6 April 2019
መጽሐፍ ቅዱሳዊ እውቀት
መጽሐፍ እንደሚል " እንግዲያስ እምነት ከመስማት ነው መስማትም በእግዚአብሔር ቃል ነው። " (ሮሜ 10፥17) በዚህ መሰረት ካለመስማት የሚጀምር እምነት እንደሌለ እንረዳለን። የወለዱንን ወላጆች ወይም ያሳደጉንን ሰዎች ሃይማኖት በመከተል ልናድግ እንችል ይሆናል ነገር ግን በማስተዋል የእድሜ ክልል ስንደርስ ስለምናምነው እምነት በቂ የሆነ እውቀት ያስፈልገናል። የእግዚአብሔርን ቃል መስማት ቀጥሎም በማወቅ እምነት እንደሚጀምር ቃሉ በግልፅ ይናገራል። በዘፈቀደ የሚኖር እምነት በእግዚአብሔር ላይ ያለ እምነት ሊሆን አይችልም።
የመጽሐፍ ቅዱስን እውቀት ወደ ጎን ያደረገ ክርስትና ሊኖር አይችልም '' ገንዘብ ላደረገው ሰው፣ እውቀት የሕይወት ምንጭ ነው '' (ምሳሌ 16፥22)። ጥያቄው ግን '' እውቀት ያስፈልጋል ወይስ አያስፈልግም ሳይሆን የያዝነው እውቀት መጽሐፍ ቅዱሳዊ ነው ወይስ ባህላዊ የአባቶች ወግ ወይስ ስርአት? '' የሚለው ነው። በመሰረቱ እውቀት ሁሉ እውነት አይደለም። ከ2000/ከ3000 ዓመት በላይ ሲወርድ ሲዋረድ የመጣም ሆነ ትላንት የገበየነው እውቀት፣ የሁለቱም ትክክለኛነት ከእግዚአብሔር ቃል አንፃር ሲጣራ እንጂ ያ እውቀት ዘመን ስለጠገበ እውነት ሊሆን አይችልም በአንፃሩም ስለዘገየም ውሸት ሊባል አይችልም። እውቀትን እውነት የሚያደርገው መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሆኑ ብቻ ነው።
እግዚአብሔርን በተሳሳተ መንገድ የሚያመልኩት ትክክለኛ እውቀት ያላቸው ሳይሆኑ እውቀት የሌላቸው ናቸው ። ጌታ እንዳለውም '' የሰውም ሥርዓት የሆነ ትምህርት እያስተማሩ በከንቱ ያመልኩኛል '' (ማቴዎስ 15፥9)። ከንቱ አምልኮ በሰው ስርአት ያለ እውቀት እግዚአብሔርን ማምለክ ነው።
'' እናንተ ከአሕዛብ ወገን ሆናችሁ ያመለጣችሁ፥ ተሰብስባችሁ ኑ በአንድነትም ቅረቡ የተቀረጸውን የምስላቸውን እንጨት የሚሸከሙና ያድን ዘንድ ወደማይችል አምላክ የሚጸልዩ እውቀት የላቸውም '' (ኢሳይያስ 45፥20)።
ያለ እግዚአብሔር ቃል እውቀት ስላሉ ሰዎች መጽሐፍ ሲናገር '' ሕዝቤ እውቀት ከማጣቱ የተነሣ ጠፍቶአልና '' (ትንቢተ ሆሴዕ 4፥6) እንደሚል ውጤቱ መጥፋት ነው። በመሆኑም በዚህ ሰዓት የእግዚአብሔርን ቃል እውቀት ችላ ብሎ ነገር ግን ራሱን አማኝ አድርጎ እያሰበ ያለ አይሳሳት። " እንግዲህ ያላመኑበትን እንዴት አድርገው ይጠሩታል? ባልሰሙትስ እንዴት ያምናሉ? " (ሮሜ 10፥14) ይላልና #በመስማት_ጀምረህ_እመን የዛሬው ምክሬ ነው።
" የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ። " (ቆላ 3፥16)
የመጽሐፍ ቅዱስን እውቀት ወደ ጎን ያደረገ ክርስትና ሊኖር አይችልም '' ገንዘብ ላደረገው ሰው፣ እውቀት የሕይወት ምንጭ ነው '' (ምሳሌ 16፥22)። ጥያቄው ግን '' እውቀት ያስፈልጋል ወይስ አያስፈልግም ሳይሆን የያዝነው እውቀት መጽሐፍ ቅዱሳዊ ነው ወይስ ባህላዊ የአባቶች ወግ ወይስ ስርአት? '' የሚለው ነው። በመሰረቱ እውቀት ሁሉ እውነት አይደለም። ከ2000/ከ3000 ዓመት በላይ ሲወርድ ሲዋረድ የመጣም ሆነ ትላንት የገበየነው እውቀት፣ የሁለቱም ትክክለኛነት ከእግዚአብሔር ቃል አንፃር ሲጣራ እንጂ ያ እውቀት ዘመን ስለጠገበ እውነት ሊሆን አይችልም በአንፃሩም ስለዘገየም ውሸት ሊባል አይችልም። እውቀትን እውነት የሚያደርገው መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሆኑ ብቻ ነው።
እግዚአብሔርን በተሳሳተ መንገድ የሚያመልኩት ትክክለኛ እውቀት ያላቸው ሳይሆኑ እውቀት የሌላቸው ናቸው ። ጌታ እንዳለውም '' የሰውም ሥርዓት የሆነ ትምህርት እያስተማሩ በከንቱ ያመልኩኛል '' (ማቴዎስ 15፥9)። ከንቱ አምልኮ በሰው ስርአት ያለ እውቀት እግዚአብሔርን ማምለክ ነው።
'' እናንተ ከአሕዛብ ወገን ሆናችሁ ያመለጣችሁ፥ ተሰብስባችሁ ኑ በአንድነትም ቅረቡ የተቀረጸውን የምስላቸውን እንጨት የሚሸከሙና ያድን ዘንድ ወደማይችል አምላክ የሚጸልዩ እውቀት የላቸውም '' (ኢሳይያስ 45፥20)።
ያለ እግዚአብሔር ቃል እውቀት ስላሉ ሰዎች መጽሐፍ ሲናገር '' ሕዝቤ እውቀት ከማጣቱ የተነሣ ጠፍቶአልና '' (ትንቢተ ሆሴዕ 4፥6) እንደሚል ውጤቱ መጥፋት ነው። በመሆኑም በዚህ ሰዓት የእግዚአብሔርን ቃል እውቀት ችላ ብሎ ነገር ግን ራሱን አማኝ አድርጎ እያሰበ ያለ አይሳሳት። " እንግዲህ ያላመኑበትን እንዴት አድርገው ይጠሩታል? ባልሰሙትስ እንዴት ያምናሉ? " (ሮሜ 10፥14) ይላልና #በመስማት_ጀምረህ_እመን የዛሬው ምክሬ ነው።
" የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ። " (ቆላ 3፥16)
Sunday, 20 January 2019
የጌታ ክብር መገለጥ (ክፍል አራት)
" ኢየሱስም። አንቺ ሴት፥ ከአንቺ ጋር ምን አለኝ? ጊዜዬ ገና አልደረሰም አላት። " (ዮሐ 2፥4)
በዚህ ቁጥር ላይ ሦስት መሰረታዊ ጥያቄዎችን በመመለስ እንዳስሳለን። እነዚህ ጥያቄዎች ለብዙ ዘመናት ሲያከራክር የቆዩና አሁንም ድረስ ብዙዎችን ያላግባቡ ጉዳዮች ናቸው።
1) አንቺ ሴት ለምን አላት?
2) ካንቺ ጋር ምን አለኝ ሲል ምን ለማለት ነው?
3) ጊዜዬ ገና አልደረሰም ምንድነው?
አንቺ ሴት:-
'' አንቺ ሴት '' የሚለውን አንዳንዶች ጌታ እናቱን ለመቃወም አድርገው ይወስዱታል ሌሎች ደግሞ የተለየ ክብር ለመስጠት የተደረገ ንግግር ነው ብለው ያምናሉ። በእኛ ባህል አንዲትን ሴት ስም እያላት አንቺ ሴት ማለት ነውር (ክብርን የሚነካ) ሊሆን ይችላል በሌለ አካባቢ ደግሞ ክብርን ሊያሳይ ይችላል። ለአብነት ያህል ነጭ ልብስ በእኛ ሀገር የደስታ ማሳያ ሲሆን በህንድ ግን የሀዘን ነው ስለሆነም ስለ ህንድ በእኛ ባህል ጆሮ መስማት የለብንም። አንቺ ሴትን ከተቻለ በእስራኤል ካልሆነ በመፅሐፍ ቅዱስ ዘይቤ መስማት አለብን። ታዲያ ጌታ እናቱ መሆኗን እያወቀ ለምን አንቺ ሴትን መረጠ? ጌታ ይህን ቃል የተጠቀመው ለመንቀፍ (ለመቃወም) ወይም የተለየ ክብር ለመስጠት መሆኑን በመፅሐፍ ቅዱስ ማስታረቅ ይኖርብናል።
ጌታ ኢየሱስ '' አንቺ ሴት '' የሚለውን አጠራር በሌላ ስፍራ ተጠቅሞታል። '' አንቺ ሴት እመኚኝ '' (ዮሐ 4፥21) እንዳለ ለሳምራዊቷ ሴት ለመንቀፍ ወይም የተለየ ክብርን ለመስጠት እንዳልጠቀመበት ማየት እንችላለን። ስለሆነም ማንኛውም የአይሁድ ወንድ ሴቶችን የሚጠራበት በባህላቸው ተቀባይነት ያለው መደበኛ አጠራር ወይም ንግግር ነው። ጌታም የተለየ ክብር መስጠት ቢፈልግ እናቴ ይላት ነበር። የድንግል ማርያም ልዩ ክብር ጌታን መውለዷ ነውና። በሌላ በኩል ማቅለል ወይም ማዋረድም እንዳይደለ በሌላ ስፍራ ጌታ ይህንኑ ቃል ለእናቱ የተጠቀመበትን ሁኔታ ማየት ይኖርብናል።
" ኢየሱስም እናቱን ይወደው የነበረውንም ደቀ መዝሙር በአጠገቡ ቆሞ ባየ ጊዜ እናቱን። አንቺ ሴት፥ እነሆ ልጅሽ አላት። " (ዮሐ 19፥26) እዚህ ጋር ጌታ ለእናቱ ያለውን መራራት ያሳያል ስለሆነም ይህ አጠራር ነቀፌታ እንደሌለው ማየት ይቻላል።
ከአንቺ ጋር ምን አለኝ:-
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክ የአንድምታው ትርጓሜ ለዚህ ክፍል በሊቃውንቶቿ የተሰጡት አንድምታዊ ትርጓሜዎች እንዲህ የሚሉ ናቸው።
ሀ) " አንድም ካንች ጋር ምን አለኝ? ማለት ውሃውን ወይን ጠጅ አድርግላቸው ብትይኝ አይሆንም እልሽ ዘንድ ካንች ጋር ምን ፀብ አለኝ? "
ይህ አተረጓጎም ሙሉ በሙሉ አዎንታዊ ነው። ኢየሱስ የእናቱን ጥያቄም ሆነ ምክንያቷን ተቀብሎ አድርጎላታል የሚል ፍቺ ያለው አተረጓጎም ነው።
ለ) " አንድም ውሃውን ጠጅ አድርግላቸው ብትዪኝ አይኾንም እልሽ ዘንድ ውሃውን ጠጅ ላላደርግላቸው ከሰርግ ቤት ተጠርቼ መጥቻለሁን? ውሃውን ጠጅ ላላደርግላቸው ነውን? አላት። "
ይህ ደግሞ የእናቱን ጥያቄ ተቀብሎም አይደለም ተገዶም አይደለም ውሃውን የወይን ጠጅ የሚያደርገው የሚል ፍቺ አለው ወይም ተአምር የሚያደርገው በእሷ ሀሳብ ላይ ተመስርቶ አይደለም የሚል አንድምታ አለው። ወደ ሰርግ ቤት የመጣሁት ይህን ላደርግ ነው እንጂ ላላደርግ አይደለም ነው።
ሐ) " አንድም ውሃውን ወይን ጠጅ አድርጌ የማጠጣቸው በኔ ፈቃድ ነው እንጂ ባንቺ ትዕዛዝ ነውን አላት "
ይህ ደግሞ ከሌሎቹ አተረጓጎም ይለያል። ጌታ ይህን ያለው በመቃወም እንደሆነና በአምላክነቱ አገብሮ (መገደድ/መታዘዝ) እንደሌለበት ለማጠየቅም (ለማረጋገጥ) እንደሆነ ነው። በማንም ትዕዛዝ የማይሰራ እንደሆነ ለማሳየት ጭምርና ውሃውን ወደ ወይን ጠጅ የማደርገው በራሴ ፈቃድ ላይ ተመስርቼ ነው የማደርገው ለማለት ነው '' ካንቺ ጋር ምን አለኝ '' ያለው ተብሎ ተተርጉሟል።
ከነዚህ አማርኛ አንድምታዊ ትርጓሜ በፊት የነበረው የግዕዝ በግዕዝ ትርጓሜ ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለድንግል ማርያም ጥያቄ የመለሰውን መልስ በተመለከተ '' አንቺ ሴት፥ ከአንቺ ጋር ምን አለኝ? ጊዜዬ ገና አልደረሰም '' የሚሉትን ሶስት ሀሳቦች ጠቅልሎ በመያዝ የሚከተለውን ማብራሪያ ሰጥቷል፡፡
" ወዘይቤሂ ኢበጽሐ ጊዜየ ዘንተ ይቤ እም ፍናወ ተግሣጽ ለእሙ ወፍካሁሰ ምንተ ትገብሪ እንበይነ ተጊሆትየ ለገቢረ ዝንቱ ተአምር፡፡ አኮ ከመ ሙሴ ወእለ ቀደሙኒ በዘመን እሙር (ዘከመ ትሩፍ ላዕሌሁ) ወባሕቱ እስመ ክሂሎትየ ላዕለ ዝንቱ ግብር ዘልፈ ውእቱ ። ጊዜ ፈቀድኩ እገበር፡፡ ወባሕቱ ኢትትላኰዪ ከመ በዝንቱ ቃል ታልዕልኒ ሶበ ሰአልክኒ ሊተ፡፡ወእመኒ ኢሰአልክኒ ሀለወኒ እግበር ወአርኢ አምላክናየ፡፡ ወበእንተዝ ጸንአት ወትቤሎሙ ለላእካን ርእዩ ዘይቤ ወግበሩ፡፡ ወይእቲሰ ለበወት እምቃሉ በአይ ጊዜ ፈቀደ ገቢረ ይገብር፡፡ ይደሉ እንከ ይኩን ቃሉ ተግሣጸ ላቲ፤ ወብሂለ ኢበጽሐ ጊዜየ እትጌበር በርእስየ ወአልብኪ ግብር ላዕሌየ፡፡ "
ትርጉም
" ጊዜዬ ገና አልደረሰም በማለቱ ለእናቱ በተግሣጽ መንገድ ተናገራት፤ ትርጕሙም ይህን ተአምር ለማድረግ እተጋ ዘንድ ምን ማድረግ ትችያለሽ? እኔ በወደድሁ ጊዜ አደርገዋለሁ ማለት ነው፡፡ ከእኔ በዘመን ቀድመው (ከእኔ በፊት) እንደነበሩ እንደ ሙሴና እንደሌሎች ነቢያት አይደለሁም፤ ነገር ግን ይህን ተአምር የማድረግ ችሎታዬ ሁልጊዜም ከእኔ ጋር ነውና በወደድሁ ጊዜ አደርገዋለሁ፤ ነገር ግን አንቺ በለመንሽ ጊዜ በዚህ በልመና ቃልሽ ታነሳሽኝ ዘንድ አትዘብዝቢኝ፤ (ደጋግመሽ አትጠይቂኝ) ባትለምኚኝም ተአምር አድርጌ አምላክነቴን እገልጥ ዘንድ አለኝ አላት፡፡ ስለዚህ እርሷ በርትታ ለአገልጋዮች የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ አለቻቸው፡፡ እርሷ ግን በወደደው በየትኛውም ጊዜ ሊያደርገው እንደሚችል አስተዋለች፤ እንኪያስ ቃሉ ለእርሷ ተግሣጽ እንደነበረ ልንረዳው ይገባል፡፡ ጊዜየ ገና አልደረሰም ማለቱም እኔ በወደድሁ ጊዜ አደርገዋለሁ፤ አንቺ ልታዝዢኝ አትችይም ማለቱ ነው፡፡ ''
እነዚህ አንድምታዊ ትርጕሞች በሙሉ አንድም የምልጃን ሐሳብ አይገልፁም። ድንግል ማርያም በእናትነትዋ ላቀረበችው ጥያቄ ጌታ የሰጣትን ምላሽ በአንድምታው መሠረት ሊቃውንቱ የሰጡት ትርጕም ምልጃዊ መልክ አላቸው ብለን ልንወስደው አያስችለንም። ይልቁንም የጌታ ምላሽ ውስጥ እርሱ ታዝዞ የሚያደርገው ነገር እንደሌለና እንደ ራሱ ሀሳብና ፈቃድ ተመስርቶ ብቻ እንደሚያደርግ የሚያሳይ ነው።
መልእክቷን ወይም ጥያቄዋን ተቀብሏል ወይስ ተቃውሞታል ለሚለው ተቀብሎታል ነገር ግን ጥያቄውን ይዛ የመጣችበትን መንገድ (Intention) ግን ተቃውሞታል። የእሷን ጥያቄ በራሱ መለኮታዊ አጀንዳ (ፕሮግራም) ውስጥ አስገባው። የእሱ ድርጊት የእሷን ጥያቄ መለሰ እንጂ የእሷ ጥያቄ እሱን ለማድረግ አላነሳሳውም (cause አላደረገውም)።
ጊዜዬ ገና አልደረሰም:-
ጊዜዬ ገና አልደረሰም ለሚለው የአንድምታ ትርጓሜ
1) ገና የወይን ጠጁ ተንጠፋጥፎ አላለቀም ለማለት እንደሆነ ጭምር ይናገራል ነገር ግን ድንግል ማርያም በቦታው አረጋግጣ ያለችው ስለሆነ ለመቀበል ይከብዳል።
2) ይሁዳ ወቶ ነበርና እስኪመለስ ድረስ እየተጠበቀ ነው የሚል ትርጉም ተሰጥቶታል። ምክንያቱም ከተአምራቱ ቢያስወጣኝ በሞቱ ገባሁበት ይላልና ተአምሩን እንዲያይ የሚል አንድምታዊ ትርጉም ተሰጥቶታል። ነገር ግን እዚህ ጋር ይሁዳ ይኑር አይኑር የሚታወቅ ነገር የለም። ይህን ፍራቻ የሚያስቀር ጌታ ይሁዳ ባለበት በተደጋጋሚ ተአምር አድርጓልና። እዚህ ጋር ይኑር አይኑርም በሌላ ስፍራ ያየው ተአምር ወይም ወንጌል ይገዛዋልና።
ጊዜዬ ገና አልደረሰም የሚለው ቃል በዚሁ በዮሐንስ ወንጌል በተደጋጋሚ ተጠቅሶ እናገኘዋለን። ለአብነት ያህልም
"፤ ኢየሱስም እንዲህ አላቸው። ጊዜዬ ገና አልደረሰም፥ ጊዜያችሁ ግን ዘወትር የተመቸ ነው። " (ዮሐ 7፥6)
"፤ ስለዚህ ሊይዙት ይፈልጉ ነበር፤ ነገር ግን ጊዜው ገና ስላልደረሰ ማንም እጁን አልጫነበትም። " (ዮሐ 7፥30)
"፤ ኢየሱስ በመቅደስ ሲያስተምር በግምጃ ቤት አጠገብ ይህን ነገር ተናገረ፤ ጊዜው ገና አልደረሰምና ማንም አልያዘውም። " (ዮሐ 8፥20)
እነዚህ በሙሉ የሚያሳዩት ጌታ ለመጣበት ዓላማ የሚያደርገውን የቤዛነት ጉዞ የሚያስረዱ ናቸው። ይህ '' ጊዜ '' የሚለው ሲደርስ ወደ ሰአት ሲቀየርም መጽሐፍ ቅዱሳችን ይናገራል።
" አሁን ነፍሴ ታውካለች ምንስ እላለሁ? አባት ሆይ፥ ከዚህ ሰዓት አድነኝ። ነገር ግን ስለዚህ ወደዚህ ሰዓት መጣሁ። " (ዮሐ 12፥27) ለዚህም ነው ቀጣዩ ምዕራፍ ሲጀምር ጌታ ከዚህ ዓለም ወደ አብ የሚሄድበት ሰዓት እንደ ደረሰ አውቆ፥ የሚለው። (ዮሐ 13፥1) ስለሆነም ጊዜዬ ገና አልደረሰም የሚለው የጌታ ምላሽ አሁንም ምላሽ እየሰጠው ነው ገና ወደ ሞት አልደረስኩም የሚል ፍቺ አለው። የማደርገው ምልክት ሞቴን ይናገራል እንጂ አሁን ጊዜዬ ገና አልደረሰም እያለ ነው።
ጌታ ኢየሱስ ከወይን ጠጅ ጉዳይ በቀጥታ ወደ ሞቱ ወሰደው። ሰርግ ቤት ሆኖ የቀራኒዬን ሞት ማሳየት ጀመረ።
" እናቱም ለአገልጋዮቹ። የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ አለቻቸው። " (ዮሐ 2፥5)
ይህ የድንግል ማርያም የእምነት ቃል ነው። ልጇ አንድ ተአምር እንደሚያደርግ ተማምናለች። የመጣችበት መንገድ ምንም ይሁን ብቻ የመጣችበት ጉዳይ ግን ሊፈፀም እንደሚችል አውቃለች። ለዚህም ነው የሚላችሁን አድርጉ ያለችው።
" አይሁድም እንደሚያደርጉት የማንጻት ልማድ ስድስት የድንጋይ ጋኖች በዚያ ተቀምጠው ነበር፥ እያንዳንዳቸውም ሁለት ወይም ሦስት እንስራ ይይዙ ነበር። " (ዮሐ 2፥6)
እዚህ ጋር ታሪኩ ሙሉ በሙሉ ከሰርግ ወደ ሃይማኖት ሲቀየር እናነባለን። ጊዜዬ ገና አልደረሰም ስንል ሞቱን እንደሆነ አይተናል ስለሆነም ይህ ሞት ደግሞ የሚለጠው ወይም የሚፈፀመው በሰርግ ሳይሆን በሃይማኖት አጀንዳ ስር ነው። ጌታም ለሰርጉ የወይን ጠጅ ማዘጋጃ ጋንን ትቶ በቀጥታ ወደ ሃይማኖት ስርአት ወደሚፈፀምባቸው ጋኖች ነው የሄደው። ጉዳዩን ከማህበራዊ አጀንዳ ወደ ሃይማኖት (መንፈሳዊ) ቀየረው። እነዚህ የመንፃት ጋኖችና ውሃ የኢየሱስ የመስሪያ ቦታ መሆኑንም እየጠቆመ ነው። ጌታ በቤተክርስቲያን ላይ በሆነው ሙሽራነቱ እንዴት ሙሽሪቱን እንደሚያነፃ እያሳየ ነው። በሞቱና በደሙ የሰውን ኃጢአት እንዴት እንደሚያነፃ እያሳየ ነበር ነገር ግን ማንም አላስተዋለም።
ይቀጥላል................
Subscribe to:
Posts (Atom)