ነገር ግን እግዚአብሔር በምሕረቱ ባለ ጠጋ ስለ ሆነ፥ ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ በበደላችን ሙታን እንኳ በሆንን ጊዜ ከክርስቶስ ጋር ሕይወት ሰጠን፥ በጸጋ ድናችኋልና፥ ኤፌ 2፥4-5
Thursday, 7 November 2019
ሥጋ የለበሰ ሁሉ
ይህም የሕግን ሥራ በመሥራት ሥጋ የለበሰ ሁሉ በእርሱ ፊት ስለማይጸድቅ ነው፤ ኃጢአት በሕግ ይታወቃልና። አሁን ግን በሕግና በነቢያት የተመሰከረለት የእግዚአብሔር ጽድቅ ያለ ሕግ ተገልጦአል (ሮሜ 3፥20-21)
በዚህ ቃል '' ሁሉ '' የሚለውን ቃል ከሰው ልጅ ፍጥረት ጀምሮ እስከ አሁን የምንኖረውን እንዲሁም ወደ ፊት የሚኖሩትንም የሰው ልጅን በሙሉ ያካተተ ነው። ታዲያ ይህ '' ሁሉ '' የሚለው ቃል ምንም እንኳን ሁለት ፊደል ቢሆንም ይህን ያህል ሰው በመወከሉ ከባድ ሀይለ ቃል ነው ማለት ማጋነን አይደለም።
ሥጋም የለበሰ ሁሉ የእግዚአብሔርን ማዳን ይይ ተብሎ እንደ ተጻፈ (ሉቃ 3፥3-6) ይህ በ''ሁሉ'' የተጠቀለለው ሥጋ ለባሽ ያለው ብቸኛ መዳኛ እግዚአብሔር ያዘጋጀው መንገድ ነው። ለዚህም መፅሐፍ ቅዱሳችን ሲናገር
" ነገር ግን ሰው በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን እንዲጸድቅ እንጂ በሕግ ሥራ እንዳይሆን አውቀን፥ ሥጋን የለበሰ ሁሉ በሕግ ሥራ ስለማይጸድቅ፥ እኛ ራሳችን በሕግ ሥራ ሳይሆን በክርስቶስ እምነት እንጸድቅ ዘንድ በክርስቶስ ኢየሱስ አምነናል። " (ገላ 2፥16) ይላል።
በመሆኑም ሥጋ ለባሽ ሆኖ በሕግ ሥራ (በሥራ) እጸድቃለው ብሎ ደፋ ቀና ቁጭ ብድግ የሚል ካለ ራሱን እንደ ሰው ማየት የተሳነው ብቻ ነው። እናም
ወገን ስማ
ባትሰማኝም ስማ
ባትወደውም ስማ
ባትፈልግም ስማ
ላልሰማም አሰማ
ዝም ብለህ አታቅማማ
በሆነው ባልሆነው ትግል አትግጠማ
በሥራ አትድንማ
እኮ በምን ሥራህ እረ ዘርዝርማ
ተው...ተው... ተው እንዳትሞክረው
ጭራሽ አታስበው
ላያድንህ ከሞት
ላያስጥልህ ከእሳት
ላያስገኝ ልጅነት
ላይኖርህ ነፃነት
ላያወጣ አርነት
ላይሆንልህ ሕይወት
ላይሰማህ እረፍት
የድንግዝግዝ ልፋት
የማትመካበት
አንተ የምታፍርበት
አንቺ የምታፍሪበት
አያድንም ከሞት
.
.
.
እኔም ዛሬ ፃፍኩት
" ሥጋን የለበሰ ሁሉ በእግዚአብሔር ፊት እንዳይመካ። " (1ኛ ቆሮ 1፥29)
Subscribe to:
Post Comments (Atom)
No comments:
Post a Comment