ነገር ግን እግዚአብሔር በምሕረቱ ባለ ጠጋ ስለ ሆነ፥ ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ በበደላችን ሙታን እንኳ በሆንን ጊዜ ከክርስቶስ ጋር ሕይወት ሰጠን፥ በጸጋ ድናችኋልና፥ ኤፌ 2፥4-5
Saturday, 1 December 2018
የሚመካ በጌታ ይመካ!
'' የሚመካ በጌታ ይመካ'' (2ኛ ቆሮ 10፥17)
ትላንት የነበረህ ነገር ዛሬ አይኖርህም። ማንም ባለበት መቀጠል እንዳይችል የተፈጥሮ ግዴታ ነው። ትናንት ላይመለስ እንደሄደ ሁሉ ዛሬም ትናንት መባሉ አይቀሬ ነውና በዛሬው ማንነትህም ላይ ራስህን አታቁም። በነበረውና ባለው በሚኖረውም አልፋ ኦሜጋ በሆነው በእግዚአብሔር ተማመን። እርሱ ከፍታና ዝቅታ የሚታዘዙለት ሁሉን ማድረግ የሚችል በኋይሉ ብዛት በችሎቱም ብርታት እንድ ስንኳ የማይታጣው፣ ከመንፈሱ የማይሰፍር ወደ ላይ ብትወጣ እርሱ በዚያ አለ፣ ወደ ታች ብትወርድ እርሱ በዚያ አለና ከእርሱ እይታ አትወጣም። እርሱ የማያንቀላፉ ቸልታ የሌለበት ተመልካች ነውና እርሱን ተመካ።
ችግር ቢመጣ ብለህ ተጠንቅቀህ ይሆናል ነገር ግን የተጠነከክለት ነገር በራሱ ከፈራከው ወጥመድ አያስመልጥክምና አትመካ። የቱንም ያህል የጥንቃቄ ሰው ብትሆን ከምታውቀውም ከማታውቀውም፣ ካስተዋልከውም ካላስተዋልከውም የጠበቀህ እርሱ ብቻ ነው። አይተህ የተሻገርከውም ሳታይ የተሻገርከውም እግዚአብሔር ፈቅዶልህ ነውና በጥበቃው እምነት ይኑርህ ያ ነውና እውነተኛ ትምክህት።
የእነ እንትና ዘመድ ነኝ ብለህ ራስህን የተሻለ አማራጭ እንዳለው ሰው አድርገህ አትቁጠር። ከሰው መዛመድ ማምለጫ አይደለም ይልቅ እግዚአብሔርን በልጁ በኢየሱስ ተወዳጀው። ገና ችግር ሳይመጣ በተጠባባቂነት የያዝከው የሰው መከታ ካለ አራግፈው ሰው የጌታ ጸጋ ካልረዳው በቀር እንኳን ለአንተ ለራሱም አይሆን። ስለ አንተ ማንም ከእግዚአብሔር ፊት የሚቆምልህ የለም ከኢየሱስ በቀር። አንተን ያለ ኢየሱስ አየህ ማለት ፍፁም በደለኛና ሞት የሚገባህ ነህ። በሕይወት ዘመንህ ሁሉ በኢየሱስ መሆንህን ለአፍታ እንኳ አትርሳው። ትምክህትህ ይህ ነው።
የፈጠረህ በዓላማ ነውና የምትኖረውም በተፈጠርክበት ዓላማ ይሁን። በዓላም የፈጠረህ እርሱ ስትቆሽሽም የሚያነፃ እርሱ ነው። አፈጣጠርህንም አነፃፅህንም ያውቅበታል። መፍጠር የእርሱ እንደሆነ ሁሉ ማዳንም ገንዘቡ ነው። እነ እከሌ የቱንም ያህል በእርሱ ፊት ሞገስ ቢኖራቸውም እነሱ እንኳ በራሳቸው በፊቱ መሆን አይችሉምና በሰው አትመካ። መጽሐፍ እንደሚል '' መላእክት ስንፍና ይከሳቸዋል ሰማያትም በፊትህ ንጽሐን አይደሉም '' እኛማ እንዴት እናድፍ ይሆን???
ሰውስ በእግዚአብሔር ፊት ጻድቅ ይሆን ዘንድ፥ ከሴትስ የተወለደ ንጹሕ ይሆን ዘንድ እንዴት ይችላል? እነሆ፥ ጨረቃ እንኳ ብሩህ አይደለም፥ ከዋክብትም በፊቱ ንጹሐን አይደሉም። ይልቁንስ ብስብስ የሆነ ሰው፥ ትልም የሆነ የሰው ልጅ ምንኛ ያንስ! (ኢዮ 25፥4-6)
ወዳጄ ትታይበት ዘንድ የተፈቀደልህ ኢየሱስ ክርስቶስ ነውና ማንንም አዳኝ አድርገህ አትመካ። መዳን በኢየሱስ ብቻ ነውና በዚህ ተመካ።
Subscribe to:
Post Comments (Atom)
No comments:
Post a Comment