ነገር ግን እግዚአብሔር በምሕረቱ ባለ ጠጋ ስለ ሆነ፥ ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ በበደላችን ሙታን እንኳ በሆንን ጊዜ ከክርስቶስ ጋር ሕይወት ሰጠን፥ በጸጋ ድናችኋልና፥ ኤፌ 2፥4-5
Friday, 7 December 2018
በሥራ መዳን
መዳን በሥራ ነው።
ነገር ግን በማን ሥራ?
እግዚአብሔር ሰማይና ምድርን በቃሉ ከፈጠረ በኋላ የሰው ልጅ በእጁ አበጀው ይህ ማለት እርሱ ሥራ ሰርቷል ለማለት ሙሉ ድፍረት ይሰጠናል። እንዲሁም ደግሞ አዳም ትዕዛዝ ከተላለፈ በኋላ ዳግም ሥራ በመስራት የቁርበትን ልብስ አለበሰው። የሰውማ ሥራ ራሱን እንኳ የማይሸፍን ከየበለስ ቅጠሎች ሰፍቶ ግልድም ማድረግ ነው (ዘፍ 3:፥7)። የእግዚአብሔር ልብስ ግን ማንነትን የሚሸፍን፣ ነውርን የሚደብቅ፣ እርግማንን የሚያርቅ ነው። ይህን ልብስ እግዚአብሔር ዝም ብሎ ከየትም አላመጣውም ይልቁንም ለሁለተኛ ጊዜ ስራ በመስራት ዳግም በእጁ ጣልቃ ገብነት ነው። እግዚአብሔር ስለ ሰው ስራ መስራት የጀመረው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ አይደለም ከፍጥረቱ ጀምሮ ነው ማዳኑም እንዲሁ። በአሮጌው ኪዳን እንደተፃፈ
" እኔ፥ እኔ እግዚአብሔር ነኝ፥ ከእኔ ሌላም የሚያድን የለም " (ኢሳ 43፥11) ያለው የሰው ልጅም ሆነ ሌላ የነፍስ ድህነትን መስጠት የሚችል ማንም ስለሌለ ነው።
እንዲሁም በአዲሱም ኪዳን መጽሐፍ ቅዱሳችን ይህን ይደግመዋል። አይደለም አንድያ ልጁ ላይ በጨከነበት በዚህ በጌታ ኢየሱስ ጸጋ ዘመን በዚያኛውም ስለ መሲሑ መምጣት በተነገረበት በጥላው ዘመንም የሚያድን አልነበረም። እግዚአብሔር እንዴት ልጁን ኢየሱስ ላይ ጨክኖ የማዳንን መንገድ በሌላ ያደርጋል ተብሎ ይታሰባል?
አዎ እግዚአብሔር ያዘጋጀው የመዳን መንገድ ሥራ ነው ነገር ግን በማን የተባለ እንደሆነ በኢየሱስ ሥራ ብቻ ነው ይለናል መጽሐፋችን።
Subscribe to:
Post Comments (Atom)
No comments:
Post a Comment