እንደተጠመቀ ከወንዝ እንደወጣ
የምወደው ልጄ የሚል ድምፅ መጣ
ልብሱ እንደረጠበ ገና ሳይደራርቅ
ጌታዬ ጸልዮ ሆነ ተአምር ድንቅ
ሰማይ ተከፈተ ታይቶ የማይታውቅ
ተልዕኮን በጸሎት ጀምሮ የዘጋ
ይተጋ ነበረ መሽቶ እስኪነጋ
ማዳኑን ሲፈፅም እንኳ በመስቀል ላይ
አላቋረጠውም ወደ አብ መጸለይ
ጎኑ እየተወጋ እየፈሰሰው ደም
አባቱን ማናገር እርሱ አላቋረጠም
ውሃ ጥም ያልገታው
ሆምጣጤ ያላስቆመው
አባቱ ሲጨክን መጣራት ያልተወው
ለሰቀሉት ሰዎች ፈፅሞ የራራው
ኢየሱስ ብቻ ነው
ሕይወቱን በትጋት ፍፁም አደረገው
በፀሎት ጀምሮ በፀሎት ጨረሰው
ተፃፈ:- ዛሬ