የጴጥሮስን ዶሮ ብዙ ጊዜ የሚጠቀሰው በፋሲካ ሰሞን ነው ነገር ግን ዛሬም በየአንዳንዱ ዛሬ ዶሮ ይጮሃል። ብዙዎቻችን በጴጥሮስ ላይ ብቻ የጮኧች አርገን እናስባለን። ዶሮዋ ጴጥሮስ ላይ መጮዋ እኛ ሕይወት ላይ ምን ፋይዳ አመጣ ብለን ካልጠየቅን ስለምን ለትምህርት ተፃፈ ማለት እንችላለን?
እርግጥ ነው ጴጥሮስ በጊዜው በራሱ ተማምኖ ሌሎች ቢሸሹ እንኳ እኔ ግን አልተውህም ብሎ ቢናገርም ያች ዶሮ እንዳትጮው ማድረግ አልቻለው። ዶሮዋ እስክትጮው ድረስ ጴጥሮስ በራስ ተማምኖ ነበር። አንዴ ካዴ ደግሞም ሁለቴ ያን እንኳ ከነበረበት የራስ መተማመን ሊባንን አልቻለም የሶስተኝው ግን የጌታ ቃል ነውና በእርግጥ ባነነ። ዛሬስ እኛ ከዚህ የምንማረው ምንድነው?
ያች ዶሮ ጴጥሮስን ወደ ንስሀ አስገሰገሰችው እናም ወዲያው በመፀፀቱና በማንባቱ በደሉ ይቅር ተባለችለት። እኛ ስንት ዓመት በየማለዳው ዶሮ ሲጮው ከነበርንበት በደልና እግዚአብሔር እንደቃሉ አለመታዘዝ ቀስቅሶን ይሆን? ይህን የራሳችን ጉድ የምናውቀው ራሳችን ነን። ስንት ዓመት የዶሮዋን ጪወት ለጴጥሮስ ብቻ አርገን አሰበነው? ዛሬም በበደል ላለ ሰው የዶሮ ጩወት ለጴጥሮስ እንደጮኧችው አይደለምን? ጪወቷን ስንሰማ ለንስሀ ማንቂያ ወይስ ከእንቅልፍ ማንቂያ?
መስማት ይሁንልን። በራሳችን ወይም በዚህ ዓለም ማስተዋል ሳይሆን በእግዚአብሔር ማስተዋል እንመላለስ ዘንድ የእርሱ መሉም ፈቃድ ይሁን። አሜን
No comments:
Post a Comment