Tuesday, 4 May 2021

የእኛ ዶሮስ?

መፅሐፍ ቅዱስ ውስጥ ያሉት ሁሉም ነገሮች ለትምህርትና ለተግሣጽ ልብንም ለማቅናት በጽድቅም ላለው ምክር ይጠቅመን ዘንድ ተፅፎልናል የቅዱሳን የሕይወት ታሪክ ጭምር (2ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 3: 16-17)። ነገር ግን ቃሉ ሊነግረን በፈለገው መጠን አንረዳውም። በሕይወት እስካላዋሃድነው ድረስ የቃሉ ጉልበት አይታወቀንም። አንዳንዴ ከታሪክ ባልዘለለ መልኩ እናየዋለን። በመፅሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተፃፈው ሁሉ በዓላማና እኛም ልንማርበት ታቅዶ ነው። በዘፈቀደ ያለ ምንም ቃል የለም። 

የጴጥሮስን ዶሮ ብዙ ጊዜ የሚጠቀሰው በፋሲካ ሰሞን ነው ነገር ግን ዛሬም በየአንዳንዱ ዛሬ ዶሮ ይጮሃል። ብዙዎቻችን በጴጥሮስ ላይ ብቻ የጮኧች አርገን እናስባለን። ዶሮዋ ጴጥሮስ ላይ  መጮዋ እኛ ሕይወት ላይ ምን ፋይዳ አመጣ ብለን ካልጠየቅን ስለምን ለትምህርት ተፃፈ ማለት እንችላለን? 

እርግጥ ነው ጴጥሮስ በጊዜው በራሱ ተማምኖ ሌሎች ቢሸሹ እንኳ እኔ ግን አልተውህም ብሎ ቢናገርም ያች ዶሮ እንዳትጮው ማድረግ አልቻለው። ዶሮዋ እስክትጮው ድረስ ጴጥሮስ በራስ ተማምኖ ነበር። አንዴ ካዴ ደግሞም ሁለቴ ያን እንኳ ከነበረበት የራስ መተማመን ሊባንን አልቻለም የሶስተኝው ግን የጌታ ቃል ነውና በእርግጥ ባነነ። ዛሬስ እኛ ከዚህ የምንማረው ምንድነው? 

ያች ዶሮ ጴጥሮስን ወደ ንስሀ አስገሰገሰችው እናም ወዲያው በመፀፀቱና በማንባቱ በደሉ ይቅር ተባለችለት። እኛ ስንት ዓመት በየማለዳው ዶሮ ሲጮው ከነበርንበት በደልና እግዚአብሔር እንደቃሉ አለመታዘዝ ቀስቅሶን ይሆን? ይህን የራሳችን ጉድ የምናውቀው ራሳችን ነን። ስንት ዓመት የዶሮዋን ጪወት ለጴጥሮስ ብቻ አርገን አሰበነው? ዛሬም በበደል ላለ ሰው የዶሮ ጩወት ለጴጥሮስ እንደጮኧችው አይደለምን? ጪወቷን ስንሰማ ለንስሀ ማንቂያ ወይስ ከእንቅልፍ ማንቂያ? 

መስማት ይሁንልን። በራሳችን ወይም በዚህ ዓለም ማስተዋል ሳይሆን በእግዚአብሔር ማስተዋል  እንመላለስ ዘንድ የእርሱ መሉም ፈቃድ ይሁን። አሜን

No comments:

Post a Comment