የሰው ልጅ ከጥፋት ውሃ ያመልጥ ዘንድ ኖህን መርከብ ስራ አለው ይህ የእግዚአብሔር ፍቃድ ነበር። የእስራኤል ህዝብ ከግብፅ ባርነት ይወጣ ዘንድ በግ አርደው የቤታቸውን የበር መቃንና ጉበን ደም እንዲቀቡት አዘዘ አመለጡም ይህም የእግዚአብሔር ፍቃድ ነበር። የሰው ልጅ ከኃጢአት ባርነት ይላቀቅ ዘንድ፣ ከዘላለም ሞት ወደ ዘላለማዊ ሕይወት ይሻገር ዘንድ፣ ከኩነኔ ወጥቶ ይጸድቅ ዘንድ፣ ከድቅድቅ ጨለማ ወደ ሚደነቅ ብርሃን ይገባ ዘንድ፣ ከሲኦል ወደ ፍቅሩ ልጅ መንግስት ይፈልስ ዘንድ፣ ልጁን ኢየሱስ ወደ ዓለም በመላክ የሁሉ ቤዛ አደረገው። ዛሬ ለእግዚአብሔር የምናቀርብለት ምስጋናና የከንፈራችን መስዋህት አዎንና አሜን በሆነው በኢየሱስ ስም ነው ይህም የእግዚአብሔር ፍቃድ ነው። ከዚህ ስም ውጪ እግዚአብሔር ምንም ነገር አይቀበልም ይህም የእግዚአብሔር ፍፁም ፈቃድ ነው። እንዲህ ተብሎ እንደተፃፈ:-
" እግዚአብሔር አብን በእርሱ እያመሰገናችሁ፥ በቃል ቢሆን ወይም በሥራ የምታደርጉትን ሁሉ በጌታ በኢየሱስ ስም አድርጉት። " (ቆላ 3፥17)
በኢየሱስ ስም ተመስገን እግዚአብሔር
በኢየሱስ ስም ከፍ በል በክብር
በኢየሱስ ስም ተባረክ አባታችን
ማደሪያህን ይክበበው ዝማሬያችን
No comments:
Post a Comment