ኢየሱስ ክርስቶስ ወደዚህ ዓለም ከመምጣቱ አስቀድሞ እውነተኛ የጽድቅ መንገድ አልታወቀም ነበር፡፡ ነገር ግን ዛሬ ሰማጣዊ አባታችን እግዚአብሔር እውነተኛውን የጽድቅ መንገድ አሳየን፡፡ ይኽውም የጽድቅ መንገድ የተባለ አንድ ልጁ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ ከሱ በቀር ሌላ ወደ ሰማያዊ አባታችን ወደ እግዚአብሔር የሚወስድ የለም፡፡ እርሱ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እኔ የእውነትና የሕይወት መንገድ ነኝ በኔ በኩል ካልሆነ በቀር አንድም ወደ አብ የሚመጣ የለም ብሎ ተናግሮዋል፡፡(ዮሐ 14÷6)ስለዚህ እኛ ሁላችን ይህንን የማያሳስት እውነተኛውን የጽድቅ መንገድ ክርስቶስን ብቻ ይዘን ከሄድን ዘወትር እየናፈቅን አባታችን ሆይ እያልን ከምንጠራው ከሰማያዊ አባታችን ከእግዚአብሔር ዘንድ ወደ ሰማያዊ ሀገራችን ወደ መንግስተ ሰማያት እንደርሳለን፤ ዳግም በስራችን እንጸድቃለን መንግስተ ሰማያት እንገባለን ብለን አንመካም፤ የምንጸድቅበት ሃይማኔታችን ክርስቶስ ብቻ ነው፡፡ ስለዚህ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ‹‹ እናንት ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ወደኔ ኑ እኔም አሳርፋችኃለሁ ቀምበሬን በላያችሁ ተሸከሙ ›› ብሏል (ማቴ 11÷58)፡፡ እንዲህም ማለቱ በእኔ ጽኑ ሲል ነው፡፡
ደግሞ ቅዱስ ጳውሎስ ጽድቅ በሃይማኖት ብቻ እንዲገኝ ስራ በመስራት እንዳይገኝ በጻፋቸው መልእክቶች ሁሉ ያስተምረናል፡፡ ‹‹ ሰው ስራ ሳይሰራ በሃይማኖት ብቻ እንዲጸድቅ እንውቃለን ›› ብሏል፡፡ (ሮሜ 3÷28) ከዚህም ቀጥሎ በ4ኛው ምዕራፍ በ4ኛውና በ5ኛው ቁጥር የሚሰራ ሰው ዋጋው አይቆጠርለትም እንዲያው እንደሚገባው ሰራ ይባላል እንጂ፡፡ የማይሰራ ግን ኃጢአተኛውን በሚያጸድቅ በእግዚአብሔር ቢያምን ማመኑ ጽድቅ ሆኖ ይቆጠርለታል ብሏል፡፡ ደግሞ ይልቁንም በጣም የሚያስረዳ በኤፌሶን መልእክቱ ‹‹ አምነን በጸጋው ድነናልና እናንተም የዳናችሁ በእግዚአብሔር ቸርነት ነው እንጂ በስራችሁ አይደለም ማንም የሚመካ እንዳይኖር ›› ብሏል (ኤፌ 2÷8-9) ዳግም ወደ ገላትያ ሰዎች በጻፈው በ2ኛው ምዕራፍ በ21ው ቁጥር ‹‹ የእግዚአብሔርን ጸጋ አልክድም የኦሪትን ስራ በመስራት የሚጸድቅ ከሆነ እንኪያስ ክርስቶስ ለከንቱ የሞተ ነዋ ›› ብሎ ተናግሮአል፡፡ ይህም ሰው ሁሉ በስራው እንዳይጸድቅ በእግዚአብሔር ጸጋና በክርስቶስ ሞት እንዲጸድቅ ያስረዳል፡፡ ክርስቶስ መሞቱ ሰው በስራው መጽደቅ የማይችል ስለ ሆነ ነው፡፡
ምንጭ:- የኢት/ኣ/ተ/ቤ/ክ '' የቤተ ክርስቲያን ጸሎት '' ከሚለው መጽሐፍ ከገጽ 93 የተገኘ።
አሜን እውነት ነው፡፡
ReplyDeleteamen
ReplyDelete